Skip to content

Amharic Quran

ከመሞትህ በፊት ቁርአንን አንብብ! (Read the holy Quran before you die!)

  • Amharic Quran
    • ድጋፍ ያድርጉልን
  • Blog
    • ቁርአንን እንረዳው
    • Quran in Oromigna

85 – Al-Burooj

Posted on December 17, 2023 By Amharic Quran No Comments on 85 – Al-Burooj
ቁርአንን እንረዳው

85 – Al-Burooj

(1) የቡርጆች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡(1) By the sky full of constellations,
(2) በተቀጠረው ቀንም፤(2) and by the promised Day,
(3) በተጣጅና በሚጣዱትም፤ (እምላለሁ)፡፡(3) and by the witness and the witnessed,
(4) የጉድቡ ባለቤቶች ተረገሙ፡፡(4) cursed be the makers of the trench,
(5) የማገዶ ባለቤት የኾነቺው እሳት (ባለቤቶች)፡፡(5) the fire full of fuel,
(6) እነርሱ በርሷ (አፋፍ) ላይ ተቀማጮች በኾኑ ጊዜ፤ (ተረገሙ)፡፡(6) when they sat around it,
(7) እነርሱም በምእምናኖቹ በሚሠሩት (ማሰቃየት) ላይ መስካሪዎች ናቸው፡፡(7) and were witnessing what they did to the believers.
(8) ከእነርሱም በአላህ አሸናፊው፣ ምስጉኑ በኾነው (ጌታ) ማመናቸውን እንጅ ሌላ ምንም አልጠሉም፡፡(8) Their only grievance against them was that they believed in Allah, the All-Mighty, the Praiseworthy,
(9) በእዚያ የሰማያትና የምድር ንግሥና ለእርሱ ብቻ በኾነው (አላህ ማመናቸውን)፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ መስካሪ ነው፡፡(9) to Whom belongs the dominion of the heavens and earth, and Allah is Witness over all things.
(10) እነዚያ ምእምንንና ምእምናትን ያሰቃዩ፣ ከዚያም ያልተጸጸቱ ለእነርሱ የገሀነም ቅጣት አልላቸው፡፡ ለእነርሱም የመቃጠሉ ስቃይ አልላቸው፡፡(10) Indeed, for those who tortured the believing men and women, then did not repent, there will be the punishment of Hell and the punishment of the burning fire.
(11) እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችንም የሠሩ ለእነርሱ ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች አሏቸው፡፡ ይህ ታላቅ ማግኘት ነው፡፡(11) But those who believed and did righteous deeds will certainly have gardens under which rivers flow; that is the supreme triumph.
(12) የጌታህ በኀይል መያዝ ብርቱ ነው፡፡(12) Indeed, the punishment of your Lord is severe.
(13) እነሆ እርሱ መፍጠርን ይጀምራል፤ ይመልሳልም፡፡(13) Indeed, it is He Who originates [the creation] then repeats it,
(14) እርሱም ምሕረተ ብዙ ወዳድ ነው፡፡(14) and He is the All-Forgiving, the Most Affectionate,
(15) የዙፋኑ ባለቤት የላቀው ነው፡፡(15) the Lord of the Glorious Throne;
(16) የሚሻውን ሁሉ ሠሪ ነው፡፡(16) He does whatever He wills.
(17) የሰራዊቶቹ ወሬ መጣልህን?(17) Has there not come to you the story of the forces
(18) የፈርዖንና የሰሙድ፤ (ወሬ)፡፡(18) of Pharaoh and Thamūd?
(19) በእውነቱ እነዚያ የካዱት በማስተባበል ውስጥ ናቸው፡፡(19) But the disbelievers are in persistent denial,
(20) አላህም በዙሪያቸው (በዕውቀቱ) ከባቢ ነው፡፡(20) although Allah encompasses them from all sides.
(21) ይልቁንም እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡(21) But this is a glorious Qur’an,
(22) የተጠበቀ በኾነ ሰሌዳ ውስጥ ነው፡፡(22) [inscribed] in a Preserved Tablet.

Post navigation

❮ Previous Post: 84 – Al-Inshiqaaq
Next Post: 86 – At-Taariq ❯

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

  • Amharic Quran
  • Blog
  • Amharic Quran
  • Blog

Copyright © 2026 Amharic Quran.

Theme: Oceanly Green by ScriptsTown