67 – Al-Mulk
67 – Al-Mulk
| (1) ያ ንግሥና በእጁ የኾነው አምላክ ችሮታው በዛ፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው፡፡ | (1) Blessed is He in Whose Hand is the dominion, and He is Most Capable of all things. |
| (2) ያ የትኛችሁ ሥራው ይበልጥ ያማረ መኾኑን ሊሞክራችሁ ሞትንና ሕይወትን የፈጠረ ነው፡፡ እርሱም አሸናፊው መሓሪው ነው፡፡ | (2) Who created death and life to test you as to which of you is best in deeds, and He is the All-Mighty, the Most Forgiving. |
| (3) ያ ሰባትን ሰማያት የተነባበሩ ኾነው የፈጠረ ነው፡፡ በአልረሕማን አፈጣጠር ውስጥ ምንም መዛነፍን አታይም፡፡ ዓይንህንም መልስ፡፡ «ከስንጥቆች አንዳችን ታያለህን?» | (3) Who created seven heavens one above another; you will not see any imperfection in the creation of the Most Compassionate. Look again; can you see any flaw? |
| (4) ከዚያም ብዙ ጊዜ ዓይንህን መላልስ፡፡ ዓይንህ ተዋርዶ እርሱም የደከመ ኾኖ ወዳንተ ይመለሳል፡፡ | (4) Then look again and again; your sight will turn back to you humbled and weary. |
| (5) ቅርቢቱን ሰማይም በእርግጥ በመብራቶች (በከዋክብት) አጌጥናት፡፡ ለሰይጣናትም መቀጥቀጫዎች አደረግናት፡፡ ለእነርሱም (ለሰይጣኖች) የእሳትን ቅጣት አዘጋጀን፡፡ | (5) We have adorned the lowest heaven with lamps and have made them as missiles to stone the devils, and We have prepared for them the punishment of the Blazing Fire. |
| (6) ለእነዚያም በጌታቸው ለካዱት የገሀነም ቅጣት አልላቸው፡፡ መመለሻይቱም ከፋች! | (6) For those who disbelieve in their Lord there will be the punishment of Hell. What a terrible destination! |
| (7) በውስጧ በተጣሉ ጊዜ፤ እርሷ የምትፈላ ስትኾን ለእርሷ (እንደ አህያ) ማናፋትን ይሰማሉ፡፡ | (7) When they are thrown in it, they will hear its roaring as it boils up, |
| (8) ከቁጭትዋ የተነሳ ልትቆራረጥ ትቀርባለች፡፡ በውስጧ ጭፍሮች በተጣሉ ቁጥር ዘበኞችዋ «አስፈራሪ (ነቢይ) አልመጣችሁምን?» በማለት ይጠይቋቸዋል፡፡ | (8) almost bursting in fury. Every time a group is thrown in it, its keepers will ask them, “Did there not come to you a warner?” |
| (9) «አይደለም በእርግጥ አስፈራሪ መጥቶናል፡፡ አስተባበልንም፡፡ አላህም ምንንም አላወረደ እናንተ (አውርዷል ስትሉ) በትልቅ ስህተት ውስጥ እንጅ አይደላችሁም አልን» ይላሉ፡፡ | (9) They will say, “Yes, a warner did come to us, but we denied and said, ‘Allah has not sent down anything; you are greatly misguided.’” |
| (10) «የምንሰማ ወይም የምናስብ በነበርንም ኖሮ በነዳጅ እሳት ጓዶች ውስጥ ባልኾን ነበር» ይላሉ፡፡ | (10) And they will say, “If only we had listened or understood, we would not be among the dwellers of the Blazing Fire.” |
| (11) በኀጢኣታቸውም ያምናሉ ለእሳት ጓዶችም (ከእዝነት) መራቅ ተገባቸው፡፡ | (11) Thus they will confess their sins. So away with the dwellers of the Blazing Fire! |
| (12) እነዚያ ጌታቸውን በሩቁ የሚፈሩ ለእነርሱ ምሕረትና ታላቅ ምንዳ አልላቸው፡፡ | (12) Indeed, those who fear their Lord unseen will have forgiveness and a great reward. |
| (13) (ሰዎች ሆይ!) ቃላችሁንም መስጥሩ፡፡ ወይም በእርሱ ጩሁ፡፡ እርሱ በልቦች ውስጥ ያለን ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡ | (13) Whether you speak secretly or openly, He is All-Knowing of that which is in the hearts. |
| (14) የፈጠረ አምላክ እርሱ ዕውቀት ረቂቁ፣ ውስጥ ዐዋቂው ሲኾን (ምስጢርን ሁሉ) አያውቅምን? | (14) Does He not know His Own creation, when He is the Most Subtle, the All-Aware? |
| (15) እርሱ ያ ምድርን ለእናንተ የተገራች ያደረገላችሁ ነው፡፡ በጋራዎችዋና በመንገዶችዋም ኺዱ፡፡፡ ከሲሳዩም ብሉ፡፡ (ኋላ) መመለሻውም ወደእርሱ ብቻ ነው፡፡ | (15) It is He Who made the earth smooth for you, so travel through its regions and eat from His provisions. And to Him is the resurrection. |
| (16) በሰማይ ውስጥ ያለን (አላህ) በእናንተ ምድርን ቢደረባባችሁ ወዲያውም እርሷ የምታረገርግ ብትኾን ትተማመናላችሁን? (አትፈሩምን?) | (16) Do you feel secure that He Who is [above] in heaven will not cause the earth to sink with you, then suddenly convulse? |
| (17) ወይም በሰማይ ውስጥ ያለን በእናንተ ላይ ጠጠርን ያዘለች ነፋስን ቢልክባችሁ ትተማመናላችሁን? (አትፈሩምን?) ማስጠንቀቄም እንዴት እንደኾነ ወደፊት ታውቃላችሁ፡፡ | (17) Do you feel secure that He Who is in heaven will not send against you a storm of stones? Only then would you know how [serious] My warning was! |
| (18) እነዚያም ከእነርሱ በፊት የነበሩት በእርግጥ አስተባበሉ፡፡ ጥላቻዬም እንዴት ነበር! | (18) Those who came before them rejected [the messengers]; then how severe was My response! |
| (19) ወደ አእዋፍ ከበላያቸው ክንፎቻቸውን ዘርግተው ተንሳፋፊዎች የሚሰበሰቡም ሲኾኑ አላዩምን? ከአልረሕማን በቀር (ባየር ላይ) የሚይዛቸው የለም፡፡ እርሱ በነገሩ ሁሉ ተመልካች ነው፡፡ | (19) Do they not see the birds above them, spreading out and folding in their wings? None holds them up except the Most Compassionate. He is indeed All-Seeing of everything. |
| (20) በእውነቱ ያ እርሱ ከአልረሕማን ሌላ የሚረዳችሁ ለእናንተ የኾነ ሰራዊት ማነው? ከሓዲዎች በመታለል ውስጥ እንጅ በሌላ ላይ አይደሉም፡፡ | (20) Which is your army that can come to your aid against the Most Compassionate? The disbelievers are in utter delusion. |
| (21) ወይም ሲሳዩን ቢይዝባችሁ ያ ሲሳይን የሚሰጣችሁ ማነው? በእውነቱ እነርሱ በሞገድና በመደንበር ውስጥ ችክ አሉ፡፡ | (21) Who is there to give you provision if He withholds His provision? Yet they persist in arrogance and aversion. |
| (22) በፊቱ ላይ ተደፍቶ የሚኼድ ሰው ይበልጥ የቀና ነውን? ወይስ በቀጥተኛ መንገድ ላይ ተስተካክሎ የሚኼድ? | (22) Who is better guided: the one who walks stumbling and falling on his face or the one who walks upright on a straight path? |
| (23) «እርሱ ያ የፈጠራችሁ ለእናንተም መስሚያና ማያዎችን፣ ልቦችንም ያደረገላችሁ ነው፡፡ ጥቂትንም አታመስግኑም» በላቸው፡፡ | (23) Say, “It is He Who brought you into being and gave you hearing, sight, and hearts; little do you give thanks.” |
| (24) «እርሱ ያ በምድር ላይ የበተናቸሁ ነው፡፡ ወደእርሱም ትሰበሰባላችሁ» በላቸው፡፡ | (24) Say, “It is He Who has dispersed you throughout the earth, and to Him you will be gathered.” |
| (25) «እውነተኞችም እንደኾናችሁ ይህ ቀጠሮ መቼ ነው?» ይላሉ፡፡ | (25) They say: “When will this promise come to pass, if you are truthful?” |
| (26) «ዕውቀቱ አላህ ዘንድ ብቻ ነው፡፡ እኔ ግልጽ አስፈራሪ እንጅ ሌላ አይደለሁም» በላቸው፡፡ | (26) Say, “That knowledge is with Allah alone, and I am only a clear warner.” |
| (27) (ቅጣቱን) ቅርብ ኾኖ ባዩትም ጊዜ የእነዚያ የካዱት ሰዎች ፊቶች ይክከፋሉ፡፡ «ይህ ያ በእርሱ ትከራከሩበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉም፡፡ | (27) Then when they see it approaching closer, the faces of the disbelievers will be distressed, and it will be said, “This is what you were asking for.” |
| (28) «አያችሁን? አላህ ቢገድለኝ ከእኔ ጋር ያሉትንም (እንደዚሁ) ወይም (በማቆየት) ቢያዝንልን ከሓዲዎችን ከአሳማሚ ቅጣት የሚያድን ማን ነው?» በላቸው፡፡ | (28) Say, “What do you think, if Allah causes me and those who are with me to die or shows us mercy, who will save the disbelievers from a painful punishment?” |
| (29) «እርሱ (እመኑበት የምላችሁ) አልረሕማን ነው፡፡ (እኛ) በእርሱ አመንን፡፡ በርሱም ላይ ተጠጋን፡፡ ወደ ፊትም በግልጽ መሳሳት ውስጥ የኾነው እርሱ ማን አንደ ኾነ በእርግጥ ታውቃላችሁ» በላቸው፡፡ | (29) Say, “He is the Most Compassionate; we believe in Him and put our trust in Him. You will come to know who is clearly misguided.” |
| (30) «አያችሁን? ውሃችሁ ሠራጊ ቢኾን ፈሳሺን ውሃ የሚያመጣላቸሁ ማን ነው?» በላቸው፡፡ (አላህ የዓለማት ጌታ ያመጣዋል)፡፡ | (30) Say, “What do you think, if your water were to sink deep into the earth, who can bring you flowing water?” |
