Default Image
11, Dec 2023
67 – Al-Mulk

67 – Al-Mulk

(1) ያ ንግሥና በእጁ የኾነው አምላክ ችሮታው በዛ፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው፡፡(1) Blessed is He in Whose Hand is the dominion, and He is Most Capable of all things.
(2) ያ የትኛችሁ ሥራው ይበልጥ ያማረ መኾኑን ሊሞክራችሁ ሞትንና ሕይወትን የፈጠረ ነው፡፡ እርሱም አሸናፊው መሓሪው ነው፡፡(2) Who created death and life to test you as to which of you is best in deeds, and He is the All-Mighty, the Most Forgiving.
(3) ያ ሰባትን ሰማያት የተነባበሩ ኾነው የፈጠረ ነው፡፡ በአልረሕማን አፈጣጠር ውስጥ ምንም መዛነፍን አታይም፡፡ ዓይንህንም መልስ፡፡ «ከስንጥቆች አንዳችን ታያለህን?»(3) Who created seven heavens one above another; you will not see any imperfection in the creation of the Most Compassionate. Look again; can you see any flaw?
(4) ከዚያም ብዙ ጊዜ ዓይንህን መላልስ፡፡ ዓይንህ ተዋርዶ እርሱም የደከመ ኾኖ ወዳንተ ይመለሳል፡፡(4) Then look again and again; your sight will turn back to you humbled and weary.
(5) ቅርቢቱን ሰማይም በእርግጥ በመብራቶች (በከዋክብት) አጌጥናት፡፡ ለሰይጣናትም መቀጥቀጫዎች አደረግናት፡፡ ለእነርሱም (ለሰይጣኖች) የእሳትን ቅጣት አዘጋጀን፡፡(5) We have adorned the lowest heaven with lamps and have made them as missiles to stone the devils, and We have prepared for them the punishment of the Blazing Fire.
(6) ለእነዚያም በጌታቸው ለካዱት የገሀነም ቅጣት አልላቸው፡፡ መመለሻይቱም ከፋች!(6) For those who disbelieve in their Lord there will be the punishment of Hell. What a terrible destination!
(7) በውስጧ በተጣሉ ጊዜ፤ እርሷ የምትፈላ ስትኾን ለእርሷ (እንደ አህያ) ማናፋትን ይሰማሉ፡፡(7) When they are thrown in it, they will hear its roaring as it boils up,
(8) ከቁጭትዋ የተነሳ ልትቆራረጥ ትቀርባለች፡፡ በውስጧ ጭፍሮች በተጣሉ ቁጥር ዘበኞችዋ «አስፈራሪ (ነቢይ) አልመጣችሁምን?» በማለት ይጠይቋቸዋል፡፡(8) almost bursting in fury. Every time a group is thrown in it, its keepers will ask them, “Did there not come to you a warner?”
(9) «አይደለም በእርግጥ አስፈራሪ መጥቶናል፡፡ አስተባበልንም፡፡ አላህም ምንንም አላወረደ እናንተ (አውርዷል ስትሉ) በትልቅ ስህተት ውስጥ እንጅ አይደላችሁም አልን» ይላሉ፡፡(9) They will say, “Yes, a warner did come to us, but we denied and said, ‘Allah has not sent down anything; you are greatly misguided.’”
(10) «የምንሰማ ወይም የምናስብ በነበርንም ኖሮ በነዳጅ እሳት ጓዶች ውስጥ ባልኾን ነበር» ይላሉ፡፡(10) And they will say, “If only we had listened or understood, we would not be among the dwellers of the Blazing Fire.”
(11) በኀጢኣታቸውም ያምናሉ ለእሳት ጓዶችም (ከእዝነት) መራቅ ተገባቸው፡፡(11) Thus they will confess their sins. So away with the dwellers of the Blazing Fire!
(12) እነዚያ ጌታቸውን በሩቁ የሚፈሩ ለእነርሱ ምሕረትና ታላቅ ምንዳ አልላቸው፡፡(12) Indeed, those who fear their Lord unseen will have forgiveness and a great reward.
(13) (ሰዎች ሆይ!) ቃላችሁንም መስጥሩ፡፡ ወይም በእርሱ ጩሁ፡፡ እርሱ በልቦች ውስጥ ያለን ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡(13) Whether you speak secretly or openly, He is All-Knowing of that which is in the hearts.
(14) የፈጠረ አምላክ እርሱ ዕውቀት ረቂቁ፣ ውስጥ ዐዋቂው ሲኾን (ምስጢርን ሁሉ) አያውቅምን?(14) Does He not know His Own creation, when He is the Most Subtle, the All-Aware?
(15) እርሱ ያ ምድርን ለእናንተ የተገራች ያደረገላችሁ ነው፡፡ በጋራዎችዋና በመንገዶችዋም ኺዱ፡፡፡ ከሲሳዩም ብሉ፡፡ (ኋላ) መመለሻውም ወደእርሱ ብቻ ነው፡፡(15) It is He Who made the earth smooth for you, so travel through its regions and eat from His provisions. And to Him is the resurrection.
(16) በሰማይ ውስጥ ያለን (አላህ) በእናንተ ምድርን ቢደረባባችሁ ወዲያውም እርሷ የምታረገርግ ብትኾን ትተማመናላችሁን? (አትፈሩምን?)(16) Do you feel secure that He Who is [above] in heaven will not cause the earth to sink with you, then suddenly convulse?
(17) ወይም በሰማይ ውስጥ ያለን በእናንተ ላይ ጠጠርን ያዘለች ነፋስን ቢልክባችሁ ትተማመናላችሁን? (አትፈሩምን?) ማስጠንቀቄም እንዴት እንደኾነ ወደፊት ታውቃላችሁ፡፡(17) Do you feel secure that He Who is in heaven will not send against you a storm of stones? Only then would you know how [serious] My warning was!
(18) እነዚያም ከእነርሱ በፊት የነበሩት በእርግጥ አስተባበሉ፡፡ ጥላቻዬም እንዴት ነበር!(18) Those who came before them rejected [the messengers]; then how severe was My response!
(19) ወደ አእዋፍ ከበላያቸው ክንፎቻቸውን ዘርግተው ተንሳፋፊዎች የሚሰበሰቡም ሲኾኑ አላዩምን? ከአልረሕማን በቀር (ባየር ላይ) የሚይዛቸው የለም፡፡ እርሱ በነገሩ ሁሉ ተመልካች ነው፡፡(19) Do they not see the birds above them, spreading out and folding in their wings? None holds them up except the Most Compassionate. He is indeed All-Seeing of everything.
(20) በእውነቱ ያ እርሱ ከአልረሕማን ሌላ የሚረዳችሁ ለእናንተ የኾነ ሰራዊት ማነው? ከሓዲዎች በመታለል ውስጥ እንጅ በሌላ ላይ አይደሉም፡፡(20) Which is your army that can come to your aid against the Most Compassionate? The disbelievers are in utter delusion.
(21) ወይም ሲሳዩን ቢይዝባችሁ ያ ሲሳይን የሚሰጣችሁ ማነው? በእውነቱ እነርሱ በሞገድና በመደንበር ውስጥ ችክ አሉ፡፡(21) Who is there to give you provision if He withholds His provision? Yet they persist in arrogance and aversion.
(22) በፊቱ ላይ ተደፍቶ የሚኼድ ሰው ይበልጥ የቀና ነውን? ወይስ በቀጥተኛ መንገድ ላይ ተስተካክሎ የሚኼድ?(22) Who is better guided: the one who walks stumbling and falling on his face or the one who walks upright on a straight path?
(23) «እርሱ ያ የፈጠራችሁ ለእናንተም መስሚያና ማያዎችን፣ ልቦችንም ያደረገላችሁ ነው፡፡ ጥቂትንም አታመስግኑም» በላቸው፡፡(23) Say, “It is He Who brought you into being and gave you hearing, sight, and hearts; little do you give thanks.”
(24) «እርሱ ያ በምድር ላይ የበተናቸሁ ነው፡፡ ወደእርሱም ትሰበሰባላችሁ» በላቸው፡፡(24) Say, “It is He Who has dispersed you throughout the earth, and to Him you will be gathered.”
(25) «እውነተኞችም እንደኾናችሁ ይህ ቀጠሮ መቼ ነው?» ይላሉ፡፡(25) They say: “When will this promise come to pass, if you are truthful?”
(26) «ዕውቀቱ አላህ ዘንድ ብቻ ነው፡፡ እኔ ግልጽ አስፈራሪ እንጅ ሌላ አይደለሁም» በላቸው፡፡(26) Say, “That knowledge is with Allah alone, and I am only a clear warner.”
(27) (ቅጣቱን) ቅርብ ኾኖ ባዩትም ጊዜ የእነዚያ የካዱት ሰዎች ፊቶች ይክከፋሉ፡፡ «ይህ ያ በእርሱ ትከራከሩበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉም፡፡(27) Then when they see it approaching closer, the faces of the disbelievers will be distressed, and it will be said, “This is what you were asking for.”
(28) «አያችሁን? አላህ ቢገድለኝ ከእኔ ጋር ያሉትንም (እንደዚሁ) ወይም (በማቆየት) ቢያዝንልን ከሓዲዎችን ከአሳማሚ ቅጣት የሚያድን ማን ነው?» በላቸው፡፡(28) Say, “What do you think, if Allah causes me and those who are with me to die or shows us mercy, who will save the disbelievers from a painful punishment?”
(29) «እርሱ (እመኑበት የምላችሁ) አልረሕማን ነው፡፡ (እኛ) በእርሱ አመንን፡፡ በርሱም ላይ ተጠጋን፡፡ ወደ ፊትም በግልጽ መሳሳት ውስጥ የኾነው እርሱ ማን አንደ ኾነ በእርግጥ ታውቃላችሁ» በላቸው፡፡(29) Say, “He is the Most Compassionate; we believe in Him and put our trust in Him. You will come to know who is clearly misguided.”
(30) «አያችሁን? ውሃችሁ ሠራጊ ቢኾን ፈሳሺን ውሃ የሚያመጣላቸሁ ማን ነው?» በላቸው፡፡ (አላህ የዓለማት ጌታ ያመጣዋል)፡፡(30) Say, “What do you think, if your water were to sink deep into the earth, who can bring you flowing water?”

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

77 – Al-Mursalaat

77 – Al-Mursalaat (1) ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣ (1) By those [winds] sent forth in succession, (2) በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣ (2) those…

62 – Al-Jumu’a

62 – Al-Jumu’a (1) በሰማያት ያለው በምድርም ያለው ሁሉ ለአላህ ንጉሥ፣ ቅዱስ፣ አሸናፊ፣ ጥበበኛ ለኾነው ያሞግሳል፡፡ (1) All that is…

104 – Al-Humaza

104 – Al-Humaza (1) ለሃሜተኛ ለዘላፊ ሁሉ ወዮለት፡፡ (1) Woe to every backbiter and slanderer, (2) ለዚያ ገንዘብን የሰበሰበና የቆጣጠረው (ያደለበውም) ለኾነ…