Default Image
10, Dec 2023
52 – At-Tur

52 – At-Tur

(1) በጡር (ጋራ) እምላለሁ፡፡(1) By the mount of Tūr,
(2) በተጻፈው መጽሐፍም፡፡(2) and by the Book inscribed
(3) በተዘረጋ ብራና ላይ፤ (በተጻፈው)፡፡(3) on an unrolled parchment,
(4) በደመቀው ቤትም፡፡(4) and by the much-frequented House [in heaven],
(5) ከፍ በተደረገው ጣራም፡፡(5) and by the canopy raised high,
(6) በተመላው ባሕርም እምላለሁ፡፡(6) and by the sea ever filled.
(7) የጌታህ ቅጣት በእርግጥ ወዳቂ ነው፤ (የማይቀር ነው)፡፡(7) The punishment of your Lord will surely come to pass;
(8) ለእርሱ ምንም ገፍታሪ የለውም፡፡(8) there is none who can avert it.
(9) ሰማይ ብርቱ መዞርን በምትዞርበት ቀን (ይኾናል)፡፡(9) On the Day when the heaven will convulse violently,
(10) ተራራዎችም መኼድን በሚኼዱበት (ቀን)፡፡(10) and the mountains will move a horrible movement,
(11) ለአስተባባዮችም ያን ጊዜ ወዮላቸው፡፡(11) then woe to the deniers on that Day,
(12) ለእነዚያ እነርሱ በውሸት ውስጥ የሚጫወቱ ለኾኑት፡፡(12) those who amuse themselves in falsehood.
(13) ወደ ገሀነም እሳት በኀይል መግገፍተርን በሚግገፈተሩበት ቀን፡፡(13) On the Day when they will be shoved into the Fire forcefully,
(14) ይህቺ ያቺ በእርሷ ታስተባብሉባት የነበራችሁት እሳት ናት፡፡(14) [They will be told,] “This is the Fire which you used to deny.
(15) ይህ (ፊት ትሉ እንደነበራችሁት) ድግምት ነውን? ወይስ እናንተ አታዩምን?(15) Is this [punishment] magic, or do you not see?
(16) ግቧት ታገሱም ወይም አትታገሡ በእናንተ ላይ እኩል ነው፡፡ የምትምመነዱት ትሠሩት የነበራችሁትን (ፍዳ) ብቻ ነው (ይባላሉ)፡፡(16) Burn in it, whether you bear it patiently or impatiently, it makes no difference to you; you are recompensed only for what you used to do.”
(17) አላህን ፈሪዎቹ በእርግጥ በገነቶችና በጸጋ ውስጥ ናቸው፡፡(17) Indeed, the righteous will be in gardens and bliss,
(18) ጌታቸው በሰጣቸው ጸጋ ተደሳቾች ኾነው (በገነት ውስጥ ናቸው)፡፡ የገሀነምንም ስቃይ ጌታቸው ጠበቃቸው፡፡(18) enjoying what their Lord has given them, and their Lord protected them from the punishment of the Blazing Fire.
(19) «ትሠሩት በነበራችሁት ምክንያት ተደሳቾች ኾናችሁ ብሉ፤ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡(19) “Eat and drink pleasantly for what you used to do,
(20) በተደረደሩ አልጋዎች ላይ ተደጋፊዎች ኾነው (በገነት ይኖራሉ)፡፡ ዓይናማዎች በኾኑ ነጫጭ ሴቶችም እናጠናዳቸዋለን፡፡(20) reclining on couches all lined up”. And We will marry them to houris with wide beautiful eyes.
(21) እነዚያም ያመኑትና ዝርያቸውም በእምነት የተከተለቻቸው ዝርያቸውን በእነርሱ እናስጠጋለን፡፡ ከሥራቸውም ምንም አናጎድልባቸውም፡፡ ሰው ሁሉ በሠራው ሥራ ተያዢ ነው፡፡(21) As for those who believe and their offspring follow them in faith, We will cause their offspring to join them, and will not detract anything from [the reward of] their deeds. Everyone will be accountable for what he earned.
(22) ከሚሹትም ሁሉ እሸትንና ስጋን እንጨምርላቸዋለን፡፡(22) And We will provide them with whatever fruit and meat they desire.
(23) በውስጧ መጠጥን ይሰጣጣሉ፡፡ በውስጧ ውድቅ ንግግርና መውወንጀልም የለም፡፡(23) They will pass around to one another a glass [of pure wine] which does not lead to idle talk or sin.
(24) ለነርሱም የኾኑ ወጣቶች ልክ የተሸፈነ ሉል መስለው በእነርሱ ላይ (ለማሳለፍ) ይዘዋወራሉ፡፡(24) They will be served by their servant boys, as if they were well-protected pearls.
(25) የሚጠያየቁ ኾነውም ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይዞራል፡፡(25) They will turn to one another with questions.
(26) «እኛ ፊት በቤተሰቦቻችን ውስጥ (ከቅጣት) ፈሪዎች ነበርን» ይላሉ፡፡(26) They will say, “Before this, we used to be in awe [of Allah] when we were living among our people.
(27) «አላህም በእኛ ላይ ለገሰ፡፡ የመርዛም እሳት ቅጣትንም ጠበቀን፡፡(27) Therefore Allah conferred favor upon us and protected us from the punishment of the Scorching Fire.
(28) «እኛ ከዚህ በፊት እንለምነው ነበርን፡፡ እነሆ እርሱ በጎ ዋይ አዛኝ ነውና» (ይላሉ)፡፡(28) Indeed, we used to call upon Him before. He is indeed the Most Kind, the Most Merciful.”
(29) (ሰዎችን) አስታውስም፡፡ አንተም በጌታህ ጸጋ ምክንያት ጠንቋይም ዕብድም አይደለህም፡፡(29) So keep exhorting [O Prophet], for you are not, by the grace of your Lord, a soothsayer or a madman.
(30) ይልቁንም የሞትን አደጋ በእርሱ የምንጠባበቅበት የኾነ ባለ ቅኔ ነው ይላሉን?(30) Or do they say: “He is a poet for whom we await a misfortune”?
(31) «ተጠባበቁ፤ እኔም ከእናንተ ጋር ከሚጠባበቁት ነኝ» በላቸው፡፡(31) Say, “Wait, I too am waiting with you.”
(32) አእምሮዎቻቸው በዚህ ያዟቸዋልን? አይደለም በእውነቱ እነርሱ ወሰን አላፊዎች ሕዝቦች ናቸው፡፡(32) Do their minds prompt them to say such things, or are they a transgressing people?
(33) ወይም «ቀጠፈው ይላሉን?» አይደለም፤ በእውነቱ አያምኑም፡፡(33) Or do they say, “He has made it [the Qur’an] up”? Rather, they are not willing to believe.
(34) እውነተኞችም ቢኾኑ መሰሉ የኾነን ንግግር ያምጡ፡፡(34) Then let them produce a discourse like this, if they are truthful.
(35) ወይስ ያለ አንዳች (ፈጣሪ) ተፈጠሩን? ወይስ እነርሱ ፈጣሪዎች ናቸውን?(35) Were they created by none, or were they the creators [of themselves]?
(36) ወይስ ሰማያትንና ምድርን ፈጠሩን? አይደለም አያረጋግጡም፡፡(36) Or did they create the heavens and earth? Rather, they are not certain in faith.
(37) ወይስ የጌታህ ግምጃ ቤቶች እነርሱ ዘንድ ናቸውን? ወይስ እነርሱ አሸናፊዎች ናቸውን?(37) Or do they possess the treasures of your Lord, or do they have full control [of everything]?
(38) ወይስ ለእነርሱ በእርሱ ላይ (ከሰማይ) የሚያዳምጡበት መሰላል አላቸውን? አድማጫቸውም (ሰማሁ ቢል) ግልጽን አስረጅ ያምጣ፡፡(38) Or do they have a stairway [to the heaven] by which they eavesdrop? Then let those who eavesdrop produce a compelling proof.
(39) ወይስ ለእርሱ ሴቶች ልጆች አሉትን? ለእናንተም ወንዶች ልጆች አሏችሁን?(39) Or does He have daughters while you have sons?
(40) ወይስ ዋጋን ትጠይቃቸዋለህን? ስለዚህ እነርሱ ከዕዳው የተከበዱ ናቸውን?(40) Or are you asking them [O Prophet] for a reward so they find it too burdensome?
(41) ወይስ ሩቁ ምስጢር እነርሱ ዘንድ ነውን? ስለዚህ እነርሱ ይጽፋሉን?(41) Or do they have [knowledge of] the unseen so they are writing it down?
(42) ወይስ ተንኮልን (ባንተ) ይሻሉን? እነዚያም የካዱት እነርሱ በተንኮል ተሸናፊዎች ናቸው፡፡(42) Or do they intend a plot [against the Prophet]? But the plot of the disbelievers will rebound against themselves.
(43) ወይስ ለእነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ አላቸውን? አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ፡፡(43) Or do they have a god other than Allah? Glory be to Allah far above what they associate with Him.
(44) ከሰማይም ቁራጭን (በእነርሱ ላይ) ወዳቂ ኾኖ ቢያዩ ኖሮ «ይህ የተደራረበ ደመና ነው» ይሉ ነበር፡፡(44) If they were to see pieces of the sky falling down, they would still say, “[This is only] a mass of clouds.”
(45) ያንንም በእርሱ የሚግገደሉበትን ቀናቸውን እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው፡፡(45) So leave them alone until they encounter their Day in which they will be struck down,
(46) ተንኮላቸው ከእነርሱ ምንንም የማይጠቅማቸውንና እነርሱም የማይርረዱበትን ቀን (እስከ ሚገናኙ ተዋቸው)፡፡(46) the Day their plots will not avail them in the least, nor will they be helped.
(47) ለእነዚያ ለበደሉትም ከዚህ ሌላ ቅርብ ቅጣት አልላቸው፡፡ ግን አብዛኛዎቻቸው አያውቁም፡፡(47) And for the wrongdoers, there will be another punishment before that, but most of them do not know.
(48) ለጌታህ ፍርድም ታገሥ፡፡ አንተ በጥበቃችን ውስጥ ነህና፡፡ ጌታህንም በምትነሳ ጊዜ ከማመስገን ጋር አወድሰው፡፡(48) Be patient [O Prophet] with your Lord’s decree, for indeed you are under Our [watchful] Eyes. And glorify the praises of your Lord when you rise.
(49) ከሌሊቱም አወድሰው፡፡ በከዋክብት መዳበቂያ ጊዜም (ንጋት ላይ አወድሰው)፡፡(49) And glorify Him at night and when the stars fade away.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

47 – Muhammad

47 – Muhammad (1) እነዚያ የካዱ ከአላህ መንገድም የከለከሉ (አላህ) ሥራዎቻቸውን አጠፋባቸው፡፡ (1) Those who disbelieve and prevent others from Allah’s way,…

16 – An-Nahl

16 – An-Nahl (1) የአላህ ትዕዛዝ መጣ፤ ስለዚህ አታስቸኩሉት፤ ከማይገባው ሁሉ ጠራ ከሚያጋሩትም ሁሉ ላቀ፤ (1) Allah’s decree is coming,…

67 – Al-Mulk

67 – Al-Mulk (1) ያ ንግሥና በእጁ የኾነው አምላክ ችሮታው በዛ፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው፡፡ (1) Blessed is…