38 – Saad
38 – Saad
| (1) ጸ. (ሷድ) የክብር ባለቤት በሆነው ቁርኣን እምላለሁ (ብዙ አማልክት አሉ እንደሚሉት አይደለም)፡፡ | (1) Sād. By the Qur’an, full of reminder, |
| (2) ይልቁንም እነዚያ የካዱት ሰዎች በትዕቢትና በክርክር ውስጥ ናቸው፡፡ | (2) yet those who disbelieve are in arrogance and dissension. |
| (3) ከእነርሱ በፊት ከክፍለ ዘመናት ሕዝቦች ብዙን አጥፍተናል፡፡ (ጊዜው) የመሸሻና የማምለጫ ጊዜ ሳይሆንም (ለእርዳታ) ተጣሩ፡፡ | (3) How many generations have We destroyed before them; they cried out when it was too late for deliverance. |
| (4) ከእነርሱ የሆነ አስፈራሪም ስለ መጣላቸው ተደነቁ፡፡ ከሓዲዎቹም «ይህ ድግምተኛ (ጠንቋይ) ውሸታም ነው» አሉ፡፡ | (4) They wonder that a warner has come to them from among themselves, and the disbelievers say, “This is a magician and a liar! |
| (5) «አማልክቶቹን አንድ አምላክ አደረጋቸውን? ይህ አስደናቂ ነገር ነው» (አሉ)፡፡ | (5) Has he made all gods into one God? Indeed, this is something strange!” |
| (6) ከእነርሱም መኳንንቶቹ «ሂዱ፤ በአማልክቶቻችሁም (መግገዛት) ላይ ታገሱ፡፡ ይህ (ከእኛ) የሚፈለግ ነገር ነውና» እያሉ አዘገሙ፡፡ | (6) The leaders among them departed, saying, “Carry on as you are, and stay faithful to your gods. Indeed, there is a motive behind it. |
| (7) «ይህንንም በኋለኛይቱ ሃይማኖት አልሰማንም፡፡ ይህ ውሸትን መፍጠር እንጅ ሌላ አይደለም» (እያሉም)፡፡ | (7) We have not heard of this in the last religion [of Christianity]. This is nothing but a fabrication. |
| (8) «ከመካከላችን በእርሱ ላይ ቁርኣን ተወረደን?» (አሉ)፡፡ በእውነት እነርሱ ከግሳጼዬ (ከቁርኣን) በመጠራጠር ውስጥ ናቸው፡፡ በእርግጥም ቅጣቴን ገና አልቀመሱም፡፡ | (8) Has the Reminder been sent down to him from among us?” Rather, they are in doubt about My Reminder, for they have not yet tasted My punishment. |
| (9) ይልቁንም የአሸናፊውና የለጋሱ ጌታህ የችሮታው መጋዘኖች እነርሱ ዘንድ ናቸውን? | (9) Or do they possess the treasuries of the mercy of your Lord, the All-Mighty, the Bestower? |
| (10) ወይስ የሰማያትና የምድር የመካከላቸውም ንግሥና የእነርሱ ነውን? (ነው ቢሉ) በመሰላሎችም ይውጡ፡፡ | (10) Or do they have the dominion of the heavens and earth and all that is between them? Then let them ascend by any means. |
| (11) እዚያ ዘንድ ከአሕዛብ የሆኑ ተሸናፊ ሰራዊት ናቸው፡፡ | (11) This is only a small army among several armies that will soon be defeated. |
| (12) ከእነርሱ በፊት የኑሕ ሕዝቦች፣ ዓድም፣ የችካሎች ባለቤት የሆነው ፈርዖንም አስተባበሉ፡፡ | (12) Before them, the people of Noah, ‘Ād, and mighty Pharaoh rejected [their prophets]; |
| (13) ሰሙድም፣ የሉጥ ሰዎችም፣ የአይከት ሰዎችም (አስተባበሉ)፡፡ እነዚህ አሕዛቦቹ ናቸው፡፡ | (13) and Thamūd and the people of Lot, and the dwellers of the Forest – such were the [denier] parties. |
| (14) ሁሉም መልክተኞቹን ያስዋሹ እንጅ ሌላ አይደሉም፡፡ ቅጣቴም ተረጋገጠባቸው፡፡ | (14) Each of them rejected their messenger, therefore My punishment became inevitable. |
| (15) እነዚህም ለእርሷ መመለስ የሌላትን አንዲትን ጩኸት እንጅ ሌላን አይጠባበቁም፡፡ | (15) They are only waiting for a single Blast that cannot be stopped. |
| (16) «ጌታችን ሆይ! ከምርመራው ቀን በፊት መጽሐፋችንን አስቸኩልልን» አሉም፡፡ | (16) They say, “Our Lord, hasten for us our share [of punishment] before the Day of Reckoning.” |
| (17) በሚሉት ነገር ላይ ታገስ፡፡ የኀይል ባለቤት የሆነውን ባሪያችንንም ዳውድን አውሳላቸው፡፡ እርሱ በጣም መላሳ ነውና፡፡ | (17) Bear with patience whatever they say, and remember Our slave David, the man of strength who constantly turned [to Allah]. |
| (18) እኛ ተራራዎችን ከቀትር በኋላና በረፋድም ከእርሱ ጋር የሚያወድሱ ሲሆኑ ገራንለት፡፡ | (18) We subjected the mountains to join him in glorifying Allah in the evening and the morning, |
| (19) በራሪዎችንም (አእዋፍን) የሚሰበሰቡ ሆነው (ገራንለት)፡፡ ሁሉም ለእርሱ (ማወደስ) የሚመላለስ ነው፡፡ | (19) and the birds, in their flocks; they all would echo his praise. |
| (20) መንግሥቱንም አበረታንለት፡፡ ጥበብንም ንግግርን መለየትንም ሰጠነው፡፡ | (20) We strengthened his kingdom, and gave him wisdom and sound judgment [and speech]. |
| (21) የተከራካሪዎቹም ወሬ መጥቶልሃልን? ምኩራቡን በተንጠላጠሉ ጊዜ፡፡ | (21) Has there come to you the story of the adversaries, when they climbed the wall of his chamber? |
| (22) በዳውድ ላይም በገቡ ጊዜ ከእነርሱም በደነገጠ ጊዜ «አትፍራ፤ (እኛ) ከፊላችን በከፊሉ ላይ ወሰን ያለፈ ሁለት ተከራካሪዎች ነን፡፡ በመካከላችንም በእውነት ፍረድ፡፡ አታዳላም፡፡ ወደ | (22) When they entered upon David, he was frightened. They said, “Do not be afraid. We are two adversaries: one of us has wronged the other, so judge between us with fairness, and do not be unjust, and guide us to the straight path. |
| (23) «ይህ ወንድሜ ነው፤ ለእርሱ ዘጠና ዘጠኝ ሴቶች በጎች አሉት፡፡ ለኔም አንዲት ሴት በግ | (23) This is my brother. He has ninety-nine ewes while I have only one. He said, ‘Give her into my charge,’ and he overpowered me in speech.” |
| (24) «ሴት በግህን ወደ በጎቹ (ለመቀላቀል) በመጠየቁ በእርግጥ በደለህ፡፡ ከተጋሪዎችም ብዙዎቹ ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ወሰን ያልፋሉ፡፡ እነዚያ ያመኑትና መልካሞችን የሠሩት ብቻ ሲቀሩ፡፡ እነርሱም በጣም ጥቂቶች ናቸው» አለ፡፡ ዳውድም የፈተንነው መኾኑን ዐወቀ፡፡ ጌታውንም ምሕረትን ለመነ፡፡ ሰጋጅ ኾኖ ወደቀም፡፡ በመጸጸት ተመለሰም፡፡ | (24) David said, “He has certainly wronged you by demanding that your ewe be added to his flock. Indeed, many partners oppress one another, except those who believe and do righteous deeds – and how few they are.” Then David realized that We were only testing him, so he asked his Lord for forgiveness, fell down bowing, and turned to Him in repentance. |
| (25) ለእርሱም እኛ ዘንድ መቅረብ (ክብር) መልካም መመለሻም አለው፡፡ | (25) So We forgave that for him, and he certainly has a place of nearness to Us and a good place of return. |
| (26) ዳውድ ሆይ! እኛ በምድር ላይ ምትክ አድርገንሃልና በሰዎች መካከል በእውነት ፍረድ፡፡ ዝንባሌሀንም አትከተል፤ከአላህ መንገድ ያሳሳትሃልና፡፡ እነዚያ ከአላህ መንገድ የሚሳሳቱ የምርመራውን ቀን በመርሳታቸው ለእነርሱ ብርቱ ቅጣት አላቸው፡፡ | (26) “O David, We have made you a ruler on earth, so judge between people with justice, and do not follow your desires lest they lead you astray from Allah’s way. Those who go astray from Allah’s way will have a severe punishment because of their forgetting the Day of Reckoning.” |
| (27) ሰማይንና ምድርን በመካከላቸውም ያለውን ሁሉ ለከንቱ አልፈጠርንም፡፡ ይህ የእነዚያ የካዱት ሰዎች ጥርጣሬ ነው፡፡ ለእነዚያም ለካዱት ሰዎች ከእሳት ወዮላቸው! | (27) We have not created the heavens and earth and all that is between them in vain. That is the assumption of those who disbelieve. So woe to the disbelievers from the Fire! |
| (28) በእውነቱ እነዚያን ያመኑትንና መልካሞችን የሠሩትን በምድር ውስጥ እንደሚያጠፉት እናደርጋለን? ወይስ አላህን ፊረዎቹን እንደ ከሓዲዎቹ እናደርጋለን? | (28) Should We make those who believe and do righteous deeds equal to those who spread corruption on earth? Or should We make the righteous equal to the wicked? |
| (29) (ይህ) ወዳንተ ያወረድነው ብሩክ መጽሐፍ ነው፡፡ አንቀጾቹን እንዲያስተነትኑና የአእምሮዎች ባለቤቶችም እንዲገሰጹ (አወረድነው)፡፡ | (29) This is a blessed Book that We have sent down to you [O Prophet] so that they may reflect upon its verses, and so that people of understanding may take heed. |
| (30) ለዳውድም ሱለይማንን ሰጠነው፡፡ ምን ያምር ባሪያ! (ሱለይማን)፣ እርሱ መላሳ ነው፡፡ | (30) And to David We gave Solomon, an excellent and faithful slave who constantly turned [to Us]. |
| (31) በእርሱ ላይ ከቀትር በኋላ በሦስት እግሮችና በአራተኛዋ ኮቴ ጫፍ የሚቆሙ ጮሌዎች ፈረሶች በተቀረቡለት ጊዜ (አስታውስ)፡፡ | (31) One evening, well-trained and swift horses of noble breed were presented before him. |
| (32) አለም «እኔ (ፀሐይ) በግርዶ እስከ ተደበቀች ድረስ ከጌታዬ ማስታወስ ፋንታ ፈረስን መውደድን መረጥኩ፡፡» | (32) He then said, “I gave preference to the love of fine things over the remembrance of my Lord,” until the sun went out of sight. |
| (33) «በእኔ ላይ መልሷት» (አለ) አጋዶችዋንና አንገቶችዋንም ማበስ ያዘ፡፡ | (33) [He ordered], “Bring them back to me,” and he began striking [their] shanks and necks. |
| (34) ሱለይማንንም በእርግጥ ፈተንነው፡፡ በመንበሩም ላይ አካልን ጣልን፡፡ ከዚያም በመጸጸት ተመለሰ፡፡ | (34) Indeed, We tested Solomon and cast upon his throne a body, then he turned [to Allah]. |
| (35) «ጌታዬ ሆይ! ለእኔ ማር፡፡ ከእኔ በኋላ ለአንድም የማይገባንም ንግሥና ስጠኝ፡፡ አንተ ለጋሱ አንተ ብቻ ነህና» አለ፡፡ | (35) He said, “My Lord, forgive me and grant me a kingdom, the like of which will never be granted to anyone after me. You are indeed the Bestower.” |
| (36) ነፋስንም በትእዛዙ ወደፈለገበት ስፍራ ልዝብ ኾና የምትፈስ ስትኾን ገራንለት፡፡ | (36) So We subjected to him the wind blowing gently by his command to wherever he wished, |
| (37) ሰይጣናትንም ገንቢዎችንና ሰጣሚዎችን ሁሉ (ገራንለት)፡፡ | (37) And [We subjected to him] the devils, all kinds of builders and divers, |
| (38) ሌሎችንም በፍንጆች ተቆራኞችን (ገራንለት)፡፡ | (38) and others bound in chains. |
| (39) «ይህ ስጦታችን ነው፡፡ ያለግምት ለግስ፤ ወይም ጨብጥ» (አልነው)፡፡ | (39) [We said], “This is Our gift, so give freely or withhold, without account.” |
| (40) ለእርሱም እኛ ዘንድ መቅረብ፤ መልካም መመለሻም በእርግጥ አልለው፡፡ | (40) And he certainly has a status of nearness to Us and a good place of return. |
| (41) ባሪያችንን አዩብንም አውሳላቸው፡፡ «እኔ ሰይጣን በጉዳትና በስቃይ ነካኝ» ሲል ጌታውን በተጣራ ጊዜ፡፡ | (41) And remember Our slave Job, when he cried out to his Lord, “Indeed, Satan has afflicted me with hardship and pain.” |
| (42) «በእግርህ (ምድርን) ምታ፡፡ ይህ ቀዝቃዛ መታጠቢያ መጠጥም ነው» (ተባለ)፡፡ | (42) [Allah said], “Stamp [the ground] with your foot: here is a cool spring for bathing and drinking.” |
| (43) ለእርሱም ከእኛ ዘንድ ለችሮታ ባለአእምሮዎችንም ለመገሠጽ ቤተሰቦቹን ከእነርሱም ጋር መሰላቸውን ሰጠነው፡፡ | (43) And We restored his family to him and the like of them as a mercy from Us and as a reminder for people of understanding. |
| (44) «በእጅህም ጭብጥ አርጩሜን ያዝ፡፡ በእርሱም (ሚስትህን) ምታ፡፡ ማላህንም አታፍርስ» (አልነው)፡፡ እኛ ታጋሸ ኾኖ አገኘነው፡፡ ምን ያምር ባሪያ እርሱ በጣም መላሳ ነው፡፡ | (44) [We said], “Take a bunch of grass in your hand, and strike [your wife] with it, and do not break your oath.” We truly found him patient – an excellent and faithful slave he was. He constantly turned [to Us]. |
| (45) ባሮቻችንንም ኢብራሂምን፣ ኢስሐቅንና ያዕቆበንም፣ የኅይልና የማስተዋል ባለቤቶች የኾኑን አውሳላቸው፡፡ | (45) Remember Our slaves: Abraham, Isaac, and Jacob – men of strength and insight. |
| (46) እኛ ጥሩ በኾነች ጠባይ መረጥናቸው፡፡ (እርሷም) የመጨረሻይቱን አገር ማስታወስ ናት፡፡ | (46) We chose them exclusively for the remembrance of the Final Home. |
| (47) እነርሱም እኛ ዘንድ ከመልካሞቹ ምርጦች ናቸው፡፡ | (47) Indeed, they are before us among the chosen and best ones. |
| (48) ኢስማዒልንም፣ አልየሰዕንም፣ ዙልኪፍልንም አውሳ፡፡ ሁሉም ከበላጮቹ ናቸው፡፡ | (48) Also remember Ishmael, Elisha, and Dhul-Kifl – all were among the best. |
| (49) ይህ መልካም ዝና ነው፡፡ ለአላህ ፈሪዎችም በእርግጥ ውብ የኾነ መመለሻ አላቸው፡፡ | (49) This is a reminder. And the righteous will surely have a good return: |
| (50) በሮቻቸው ለእነርሱ የተከፈቱ ሲኾኑ የመኖሪያ ገነቶች አሏቸው፡፡ | (50) Gardens of Eternity, with gates wide open for them. |
| (51) በእርሷ ውስጥ የተደገፉ ኾነው በውስጧ በብዙ እሸቶችና በመጠጥም ያዝዛሉ፡፡ | (51) They will recline therein, calling for abundant fruit and drink. |
| (52) እነርሱ ዘንድም ዓይኖቻቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች እኩያዎች (ሴቶች) አልሉ፡፡ | (52) And they will have maidens of modest gaze and equal age. |
| (53) ይህ ለምርመራው ቀን የምትቀጠሩት ተሰፋ ነው፡፡ | (53) This is what you are promised for the Day of Account. |
| (54) ይህ ሲሳያችን ነው፡፡ ለእርሱ ምንም ማለቅ የለውም፡፡ | (54) Indeed, this is Our provision [for the righteous] that will never cease. |
| (55) ይህ (ለአማኞች ነው)፡፡ ለጠማሞችም በጣም የከፋ መመለሻ አላቸው፡፡ | (55) This [is so]. But the transgressors will surely have the worst return: |
| (56) የሚገቧት ስትኾን ገሀነም (አለቻቸው)፡፡ ምንጣፊቱም ምንኛ ከፋች፡፡ | (56) Hell, where they will burn. What a terrible resting place! |
| (57) ይህ (ለከሓዲዎች ነው)፡፡ ይቅመሱትም፡፡ የፈላ ውሃና እዥ ነው፡፡ | (57) Let them taste this: scalding water and pus, |
| (58) ሌላም ከመሰሉ ዓይነቶች አልሉ፡፡ | (58) and other similar [torments] of various kinds. |
| (59) ይህ ከእናንተ ጋር በመጋፈጥ ገቢ ጭፍራ ነው፤ (ይባላሉ)፡፡ ለእነርሱ አይስፋቸው፡፡ እነርሱ እሳትን ገቢዎች ናቸውና (ይላሉ)፡፡ | (59) [The misleaders will say], “Here is a crowd of people being thrown in with you. There is no welcome for them; they will surely burn in the Fire.” |
| (60) (ተከታዮቹ) ይላሉ «ይልቁን እናንተ አይስፋችሁ፡፡ እናንተ (ክህደቱን) ለእኛ አቀረባችሁት፡፡ መርጊያይቱም (ገሀነም) ከፋች፡፡» | (60) They will say, “No, it is you for whom there is no welcome! You brought this on us. What a terrible place to settle in!” |
| (61) «ጌታችን ሆይ! ይህንን ያቀረበልንን ሰው በእሳት ውስጥ እጥፍን ቅጣት ጨምርለት» ይላሉ፡፡ | (61) They will say, “Our Lord, whoever brought this on us, give him double punishment in the Fire.” |
| (62) ይላሉም «ለእኛ ምን አለን? ከመጥፎዎች እንቆጥራቸው የነበሩትን ሰዎች (እዚህ) አናይምሳ፡፡» | (62) They will say, “Why do we not see those whom we considered to be among the wicked? |
| (63) «መቀለጃ አድርገን ያዝናቸውን? ወይስ ዓይኖቻችን ከእነሱ ዋለሉ?» | (63) Is it that we mistakenly made fun of them, or do our eyes fail to see them [in the Fire]?” |
| (64) ይህ በእርግጥ እምነት ነው፡፡ (እርሱም) የእሳት ሰዎች (የእርስ በእርስ) መካሰስ ነው፡፡ | (64) This is certainly true that the people of the Fire will dispute among themselves. |
| (65) «እኔ አስፈራሪ ብቻ ነኝ፡፡ ኀያል አንድ ከኾነው አላህ በቀር ምንም አምላክ የለም» በላቸው፡፡ | (65) Say [O Prophet], “I am only a warner, and none has the right to be worshiped except Allah, the One, the Subjugator, |
| (66) «የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ አሸናፊው መሓሪው ነው፡፡» | (66) Lord of the heavens and earth and all that is between them, the All-Mighty, Most Forgiving.” |
| (67) በላቸው «እርሱ (ቁርኣን) ታላቅ ዜና ነው፡፡ | (67) Say, “This [Qur’an] is of great importance |
| (68) «እናንተ ከእርሱ ዘንጊዎች ናችሁ፡፡ | (68) from which you are turning away.” |
| (69) (በአደም ነገር) «በሚከራከሩ ጊዜ በላይኛው ሰራዊት ለእኔ ምንም ዕውቀት አልነበረኝም፡፡ | (69) [And say], “I had no knowledge of the highest assembly [of angels] when they were disputing [about Adam]. |
| (70) «ወደእኔም አስፈራሪ ገላጭ መኾኔ እንጂ ሌላ አይወረድልኝም» (በል)፡፡ | (70) I have only received revelation in order to give a clear warning.” |
| (71) ጌታህ «ለመላእክት እኔ ሰውን ከጭቃ ፈጣሪ ነኝ ባለ ጊዜ» (አስታውስ)፡፡ | (71) [Remember] when your Lord said to the angels, “I am going to create a human being from clay. |
| (72) «ፍጥረቱንም ባስተካከልኩና ከመንፈሴ በነፋሁበት ጊዜ ለእርሱ ሰጋጆች ኾናችሁ ውደቁ» (አልኩ)፡፡ | (72) When I completed his creation and breathed into him of My spirit, fall down in prostration to him.” |
| (73) መላእክትም መላውም ባንድነት ሰገዱ፡፡ | (73) Then the angels fell down in prostration all together, |
| (74) ኢብሊስ ብቻ ሲቀር፡፡ ኮራ፤ ከከሓዲዎቹም ነበር፡፡ | (74) except Iblīs, who was arrogant and became one of the disbelievers. |
| (75) (አላህም) «ኢብሊስ ሆይ! በሁለት እጆቼ (በኃይሌ) ለፈጠርኩት ከመስገድ ምን ከለከለህ? (አሁን) ኮራህን? ወይስ (ፊቱኑ) ከትዕቢተኞቹ ነበርክ?» አለው፡፡ | (75) [Allah] said, “O Iblīs, what prevented you from prostrating to whom I created with My two Hands? Did you just become proud or have you always been arrogant?” |
| (76) «እኔ ከእርሱ በላጭ ነኝ፡፡ ከእሳት ፈጠርከኝ፤ ከጭቃም ፈጠርከው» አለ፡፡ | (76) He said, “I am better than him: You created me from fire and created him from clay.” |
| (77) (አላህ) አለው «ከእርሷ ውጣ፤ አንተ የተባረርክ ነህና፡፡» | (77) [Allah] said, “Then get out of here, for you are accursed, |
| (78) «እርግማኔም እስከ ፍርዱ ቀን ድረስ ባንተ ላይ ይኹን፡፡» | (78) and My curse will be upon you until the Day of Judgment.” |
| (79) «ጌታዬ ሆይ! እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ አቆየኝም» አለ፡፡ | (79) He said, “My Lord, then give me respite until the Day of their resurrection.” |
| (80) (አላህም) አለው «አንተ ከሚቆዩት ነህ፡፡» | (80) Allah said, “You are given respite, |
| (81) «እስከ ታወቀው ወቅት ቀን ድረስ፡፡» | (81) until the Day of the appointed time.” |
| (82) (እርሱም) አለ «በአሸናፊነትህ ይኹንብኝ፤ በመላ አሳስታቸዋለሁ፡፡» | (82) Iblīs said, “By Your Might, I will surely mislead them all, |
| (83) «ከእነርሱ ምርጥ የኾኑት ባሮችህ ብቻ ሲቀሩ፡፡» | (83) except Your chosen slaves among them.” |
| (84) (አላህ) አለው «እውነቱም (ከኔ ነው)፡፡ እውነትንም እላለሁ፡፡ | (84) Allah said, “Such is the truth – and I only say the truth – |
| (85) ከአንተና ከእነርሱ ውስጥ ከተከተሉህ ባንድ ላይ ገሀነምን በእርግጥ እሞላታለሁ፡፡» | (85) that I will certainly fill Hell with you and those of them who follow you all together.” |
| (86) በላቸው «በእርሱ ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፤ እኔም ከተግደርዳሪዎቹ አይደለሁም፡፡ | (86) Say [O Prophet], “I do not ask you for any reward for it, nor do I pretend to be what I am not. |
| (87) «እርሱ (ቁርኣን) ለዓለማት መገሠጫ እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ | (87) It is only a reminder for all people. |
| (88) «ትንቢቱንም (እውነት መኾኑን) ከጊዜ በኋላ በእርግጥ ታውቁታላችሁ፡፡» | (88) And you will surely know its truth after a while.” |
