Default Image
17, Dec 2023
82 – Al-Infitaar

82 – Al-Infitaar

(1) ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤(1) When the sky breaks apart.
(2) ከዋክብትም ተበታትነው በወደቁ ጊዜ፤(2) and when the stars fall, scattered,
(3) ባሕሮችም በተከፈቱና በተደበላለቁ ጊዜ፤(3) and when the seas burst forth,
(4) መቃብሮችም በተገለባበጡና (ሙታን) በተነሱ ጊዜ፤(4) and when the graves are overturned,
(5) ማንኛይቱም ነፍስ ያስቀደመችውንና ያቆየችውን ታውቃለች፡፡(5) then each soul will come to know what it has done or what it has left undone.
(6) አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ?(6) O mankind, what has lured you away from your Lord, the Most Generous,
(7) በዚያ በፈጠረህ አካለ ሙሉም ባደረገህ ባስተካከለህም፡፡(7) Who created you, then shaped and proportioned you,
(8) በማንኛውም በሻው ቅርፅ በገጣጠመህ (ጌታህ ምን አታለለህ)፡፡(8) and assembled you in whatever form He willed?
(9) ተከልከሉ፤ በእውነቱ በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ፡፡(9) No indeed; but you deny the Judgment Day,
(10) በእናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትኾኑ፤(10) while there are watchers over you,
(11) የተከበሩ ጸሐፊዎች የኾኑ፤ (ተጠባባቂዎች)፡፡(11) honorable scribes,
(12) የምትሠሩትን ሁሉ የሚያውቁ፡፡(12) who know whatever you do.
(13) እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በገነት ውስጥ ናቸው፡፡(13) Indeed, the righteous will be in Bliss,
(14) ከሓዲዎቹም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው፡፡(14) and the wicked will be in the Blazing Fire,
(15) በፍርዱ ቀን ይገቧታል፡፡(15) which they will enter on Judgment Day,
(16) እነርሱም ከርሷ ራቂዎች አይደሉም፡፡(16) and will never come out of it.
(17) የፍርድ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?(17) How do you know what Judgment Day is?
(18) ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?(18) Again, how do you know what Judgment Day is?
(19) (እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግን የማትችልበት ቀን ነው፡፡ ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው፡፡(19) It is the Day when no soul will be of any help to another, and all command on that Day will be with Allah.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

104 – Al-Humaza

104 – Al-Humaza (1) ለሃሜተኛ ለዘላፊ ሁሉ ወዮለት፡፡ (1) Woe to every backbiter and slanderer, (2) ለዚያ ገንዘብን የሰበሰበና የቆጣጠረው (ያደለበውም) ለኾነ…

51 – Adh-Dhaariyat

51 – Adh-Dhaariyat (1) መበተንን በታኞች በኾኑት (ነፋሶች)፡፡ (1) By the winds that scatters [dust], (2) ከባድ (ዝናምን) ተሸካሚዎች በኾኑትም (ደመናዎች)፡፡ (2) and by the…

66 – At-Tahrim

66 – At-Tahrim (1) አንተ ነቢዩ ሆይ! አላህ ለአንተ የፈቀደልህን ነገር ሚስቶችህን ማስወደድን የምትፈልግ ስትኾን (ባንተ ላይ) ለምን እርም ታደርጋለህ? አላህም እጅግ…