Default Image
10, Dec 2023
51 – Adh-Dhaariyat

51 – Adh-Dhaariyat

(1) መበተንን በታኞች በኾኑት (ነፋሶች)፡፡(1) By the winds that scatters [dust],
(2) ከባድ (ዝናምን) ተሸካሚዎች በኾኑትም (ደመናዎች)፡፡(2) and by the heavily-laden clouds with water,
(3) ገር (መንሻለልን) ተንሻላዮች በኾኑትም (መርከቦች)፡፡(3) and by the ships that sail with ease,
(4) ነገርን ሁሉ አከፋፋዮች በኾኑትም (መላእክት) እምላለሁ፡፡(4) and by the angels who distribute [blessings] by His command.
(5) የምትቀጠሩት (ትንሣኤ) እውነት ነው፡፡(5) Indeed, what you are promised is true,
(6) (እንደየሥራው) ዋጋን ማግኘትም፤ ኋኝ ነው፤ (የማይቀር ነው)፡፡(6) and the Judgment will surely come to pass.
(7) የ(ከዋክብት) መንገዶች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡(7) By the heaven with its pathways,
(8) እናንተ (የመካ ሰዎች) በተለያየ ቃል ውስጥ ናችሁ፡፡(8) Indeed, you [Makkans] have conflicting views [about the truth].
(9) ከርሱ የሚዝዞር ሰው ይዝዞራል፡፡(9) He who is diverted from it is destined to be diverted.
(10) በግምት የሚናገሩ ውሸታሞች ተረገሙ፡፡(10) Doomed are those who base their beliefs on conjecture.
(11) እነዚያ እነርሱ በሚሸፍን ስሕተተ ውስጥ ዘንጊዎች የኾኑት፡፡(11) those who are steeped in ignorance heedlessly.
(12) የዋጋ መስጫው ቀን መቼ እንደ ኾነ ይጠይቃሉ፡፡(12) They ask [mockingly], “When is the Day of Judgment?”
(13) (እነርሱ) በእሳት ላይ በሚፈተኑበት ቀን ነው፡፡(13) It is the Day when they will be punished by the Fire.
(14) «መከራችሁን ቅመሱ፤ ይህ ያ በእርሱ ትቻኮሉበት የነበራችሁት ነው» (ይባላሉ)፡፡(14) [It will be said], “Taste your punishment! This is what you were seeking to hasten.”
(15) አላህን ፈሪዎቹ በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡(15) Indeed, the righteous will be in gardens and springs,
(16) ያንን ጌታቸው የሰጣቸውን ተቀባዮች ኾነው፤ (በገነት ውስጥ ይኾናሉ)፡፡ እነርሱ ከዚህ በፊት መልካም ሰሪዎች ነበሩና፡፡(16) receiving what their Lord will give them, for they were indeed doers of good beforehand.
(17) ከሌሊቱ ጥቂትን ብቻ ይተኙ ነበሩ፡፡(17) They used to sleep but little at night,
(18) በሌሊቱ መጨረሻዎችም እነርሱ ምሕረትን ይለምናሉ፡፡(18) and before dawn they would seek forgiveness,
(19) በገንዘቦቻቸውም ውስጥ ለለማኝና (ከልመና) ለተከለከለም (በችሮታቸው) መብት አልለ፡፡(19) and in their wealth, there was a share for the beggar and the destitute.
(20) በምድርም ውስጥ ለሚያረጋግጡ ሰዎች ምልክቶች አልሉ፡፡(20) On earth there are signs for those who are certain in faith,
(21) በነፍሶቻችሁም ውስጥ (ምልክቶች አልሉ)፤ ታዲያ አትመለከቱምን?›(21) and also within yourselves. Do you not see?
(22) ሲሳያችሁም የምትቀጠሩትም (ፍዳና ምንዳ) በሰማይ ውስጥ ነው፡፡(22) And in the heaven is your provision and all that you are promised.
(23) በሰማይና በምድር ጌታም እምላለሁ፡፡ እርሱ እናንተ እንደምትናገሩት ብጤ እርግጠኛ ነው፡፡(23) By the Lord of the heaven and earth, this [resurrection] is certainly as true as the fact that you can speak.
(24) የተከበሩት የኢብራሂም እንግዶች ወሬ መጥቶሃልን?(24) Has there come to you the story of Abraham’s honored guests?
(25) በእርሱ ላይ በገቡና «ሰለም» ባሉ ጊዜ (አስታውስ)፡፡ «ሰላም ያልታወቃችሁ ሕዝቦች ናችሁ፤» አላቸው፡፡(25) When they came to him and said, “Peace.” He said, “Upon you be peace.” [saying to himself] “Unknown people!”
(26) ወደ ቤተሰቡም ተዘነበለ፤» ወዲያውም የሰባ ወይፈንን አመጣ፡፡(26) Then he went quickly to his household, and came with a fat [roasted] calf,
(27) ወደእነርሱም (አርዶና ጠብሶ) አቀረበው፡፡ «አትበሉም ወይ?» አላቸው፡፡(27) and placed it before them and said, “Will you not eat?”
(28) ከእነርሱ መፍራትንም በልቡ አሳደረ፡፡ «አትፍራ» አሉት፡፡ በዐዋቂ ወጣት ልጅም አበሰሩት፡፡(28) He felt apprehensive about them. They said, “Do not be afraid,” and gave him glad tidings of a knowledgeable son.
(29) ሚስቱም እየጮኸች መጣች፡፡ ፊቷንም መታች፡፡ «መካን አሮጊት ነኝ» አለችም፡፡(29) His wife cried out loud, and struck her face [in astonishment] and said, “[I am] a barren old woman!”
(30) እንደዚህ ጌታሽ ብሏል፡፡ «እነሆ እርሱ ጥበባ ዐዋቂ ነውና» አሏት፡፡(30) They said, “This is what your Lord said. Indeed, He is the All-Wise, the All-Knowing.”
(31) «እናንተ መልክተኞች ሆይ! ታዲያ ነገራችሁ ምንድን ነው?» አላቸው፡፡(31) Abraham said, “Then what is your mission, O messengers?”
(32) (እነርሱም) አሉ፡- «እኛ ወደ አመጸኞች ሕዝቦች ተልከናል፡፡»(32) They said, “We have been sent to a wicked people,
(33) በእነርሱ ላይ ከጭቃ የኾኑን ድንጋዮች ልንለቅባቸው (ተላክን)፡፡(33) to send down upon them stones of clay,
(34) በጌታህ ዘንድ ለድንበር አላፊዎቹ (በየስማቸው) ምልክት የተደረገባት ስትኾን፡፡(34) marked by your Lord for the transgressors.”
(35) ከምእምናንም፤ በእርሷ (በከተማቸው) ውስጥ የነበሩትን አወጣን፡፡(35) We brought out those believers who were there,
(36) በውስጧም ከሙስሊሞች ከአንድ ቤት (ቤተሰቦች) በስተቀር አላገኘንም፡፡(36) but We only found in it one Muslim household [Lot’s family].
(37) በውስጧም ለእነዚያ አሳማሚውን ቅጣት ለሚፈሩት ምልክትን አስቀረን፡፡(37) And We left there a sign [as a lesson] for those who fear the painful punishment.
(38) በሙሳም (ወሬ) ውስጥ ወደ ፈርዖን በግልጽ ማስረጃ በላክነው ጊዜ (ምልክትን አደረግን)፡፡(38) And [there is a sign in the story of] Moses when We sent him to Pharaoh with compelling proofs,
(39) ከድጋፉ (ከሰራዊቱ) ጋርም (ከእምነት) ዞረ፡፡ (እርሱ) «ድግምተኛ ወይም ዕብድ ነው» አለም፡፡(39) But he and his supporters turned away, and he said about [Moses], “A magician or a madman!”
(40) እርሱንም ሰራዊቱንም ያዝናቸው፡፡ እርሱ ተወቃሽ ሲኾን በባሕር ውስጥም ጣልናቸው፡፡(40) So We seized him and his soldiers, and cast them into the sea while he was blameworthy.
(41) በዓድም በእነርሱ ላይ መካንን ነፋስ በላክን ጊዜ (ምልክት አልለ)፡፡(41) And [there is a sign in the story of] ‘Ād, when We sent against them the devastating barren wind.
(42) በላዩ ላይ የመጣችበትን ማንኛውንም ነገር እንደ በሰበሰ አጥንት ያደረገችው ብትኾን እንጂ አትተወውም፡፡(42) It spared nothing it came upon except that it reduced it to ruin and decay.
(43) በሰሙድም ለእነርሱ «እስከ ጊዜ (ሞታችሁ) ድረስ ተጣቀሙ» በተባሉ ጊዜ (ምልክት አልለ)፡፡(43) And [there is a sign in the story of] Thamūd, when they were told, “Enjoy yourselves for a while.”
(44) ከጌታቸው ትዕዛዝም ኮሩ፡፡ እነርሱም እያዩ ጩኸት ያዘቻቸው፡፡(44) But they rebelled against the command of their Lord, so the thunderbolt seized them, while they were looking on.
(45) መቆምንም ምንም አልቻሉም፡፡ የሚርረዱም አልነበሩም፡፡(45) They could not withstand it, nor could they ward it off.
(46) የኑሕንም ሕዝቦች ከዚህ በፊት (አጠፋን)፡፡ እነርሱ አመጸኞች ሕዝቦች ነበሩና፡፡(46) And the people of Noah [were also destroyed] before them. They were indeed a rebellious people.
(47) ሰማይንም በኀይል ገነባናት፡፡ እኛም በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡(47) We built the heaven with might, and We are indeed expanding it.
(48) ምድርንም ዘረጋናት፡፡ ምን ያማርንም ዘርጊዎች (ነን!)(48) And We spread out the earth. How well did We smooth it out!
(49) ትገነዘቡም ዘንድ ከነገሩ ሁሉ ሁለት (ተቃራኒ) ዓይነትን ፈጠርን፡፡(49) And We have created everything in pairs, so that you may take heed.
(50) «ወደ አላህም ሽሹ፤ እኔ ለእናንተ ከርሱ ግልጽ አስጠንቃቂ ነኝና» (በላቸው)፡፡(50) So flee to Allah. Indeed, I am a clear warner to you from Him.
(51) ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አታድርጉ፡፡ እኔ ለእናንተ ከእርሱ (የተላክሁ) ግልጽ አስፈራሪ ነኝና፡፡(51) And do not set up another god with Allah. Indeed, I am a clear warner to you from Him.”
(52) (ነገሩ) እንደዚሁ ነው፡፡ እነዚያን ከእነርሱ በፊት የነበሩትን ከመልክተኛ ማንም አልመጣቸውም፡፡ (እርሱ) «ድግምተኛ ወይም ዕብድ ነው» ያሉ ቢኾኑ እንጂ፡፡(52) Likewise, no messenger came to those before them without being told: “A magician, or a madman!”
(53) በእርሱ (በዚህ ቃል) አደራ ተባብለዋልን? አይደለም፤ እነርሱ ጥጋበኞች ሕዝቦች ናቸው፡፡(53) Did they suggest this to one another? Rather they are a transgressing people.
(54) ከእነርሱም (ክርክር) ዘወር በል፤ (ተዋቸው)፡፡ አንተ ምንም ተወቃሽ አይደለህምና፡፡(54) So turn away from them [O Prophet], for you are not to blame.
(55) ገሥጽም፤ ግሣጼ ምእመናንን ትጠቅማለችና፡፡(55) But keep reminding them, for reminder benefits the believers.
(56) ጋኔንንና ሰውንም ሊግገዙኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም፡፡(56) I have not created the jinn and mankind except to worship Me.
(57) ከነርሱም ምንም ሲሳይ አልፈልግም፡፡ ሊመግቡኝም አልሻም፡፡(57) I seek no provision from them, nor do I want them to feed Me.
(58) አላህ እርሱ ሲሳይን ሰጪ የብርቱ ኀይል ባለቤት ነው፡፡(58) Indeed, it is Allah Who is the All-Provider, Lord of Power, the Mighty.
(59) ለእነዚያም ለበደሉት እንደ ጓደኞቻቸው ፋንታ ብጤ (የቅጣት) ፋንታ አልላቸው፡፡ ስለዚህ አያስቸኩሉኝ፡፡(59) Indeed, those who do wrong will have a share [of punishment] like that of their predecessors, so let them not ask Me to hasten it.
(60) ለነዚያም ለካዱት ከዚያ ከሚቀጠሩት ቀናቸው ወዮላቸው፡(60) So woe to those who disbelieve from [the punishment of] the Day which they are promised.     

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

48 – Al-Fath

48 – Al-Fath (1) እኛ ላንተ ግልጽ የኾነን መክፈት ከፈትንልህ፡፡ (1) Indeed, We have given you [O Prophet] a clear victory, (2)…

23 – Al-Muminoon

23 – Al-Muminoon (1) ምእምናን ፍላጎታቸውን ሁሉ በእርግጥ አገኙ (ዳኑ)፡፡ (1) The believers have attained true success: (2) እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው…

106 – Quraish

106 – Quraish (1) ቁረይሽን ለማላመድ (ባለዝሆኖቹን አጠፋ)፡፡ (1) For the accustomed security of the Quraysh, (2) የብርድና የበጋን ወራት ጉዞ…