Default Image
19, Dec 2023
88 – Al-Ghaashiya

88 – Al-Ghaashiya

(1) የሸፋኝቱ (ትንሣኤ) ወሬ መጣህን? (1) Has there come to you the story of the Overwhelming Event?
(2) ፊቶች በዚያ ቀን ተዋራጆች ናቸው፡፡ (2) On that Day, some faces will be humiliated,
(3) ሠሪዎች ለፊዎች ናቸው፡፡ (3) toiling and weary,
(4) ተኳሳን እሳት ይገባሉ፡፡ (4) as they burn in a scorching Fire.
(5) በጣም ከፈላች ምንጭ ይጋታሉ፡፡ (5) They will be made to drink from a boiling spring,
(6) ለእነርሱ ዶሪዕ ከሚባል (እሾሃም) ዛፍ እንጅ ሌላ ምግብ የላቸውም፡፡ (6) and they will have no food except bitter thorny plants,
(7) የማያሰባ ከረኃብም የማያብቃቃ ከኾነው፡፡ (7) that neither nourishes nor satisfies hunger.
(8) ፊቶች በዚያ ቀን ተቀማጣዮች ናቸው፡፡ (8) Other faces on that Day will be joyful,
(9) ለሥራቸው ተደሳቾች ናቸው፡፡ (9) well-pleased with their past striving,
(10) በከፍተኛ ገነት ውስጥ ናቸው፡፡ (10) in an elevated garden,
(11) በውስጧ ውድቅን ነገር አይሰሙም፡፡ (11) wherein no idle talk will be heard.
(12) በውስጧ ፈሳሾች ምንጮች አልሉ፡፡ (12) There will be a flowing spring;
(13) በውስጧ ከፍ የተደረጉ አልጋዎች አልሉ፡፡ (13) and couches raised high,
(14) በተርታ የተኖሩ ብርጭቆዎችም፡፡ (14) and cups placed ready,
(15) የተደረደሩ መከዳዎችም፡፡ (15) and cushions lined up,
(16) የተነጠፉ ስጋጃዎችም (አልሉ)፡፡ (16) and splendid carpets spread out.
(17) (ከሓዲዎች) አይመለከቱምን? ወደ ግመል እንዴት እነደተፈጠረች! (17) Do they not reflect on the camel, how it is created;
(18) ወደ ሰማይም እንዴት ከፍ እንደ ተደረገች! (18) and the sky, how it is raised high;
(19) ወደ ተራራዎችም እንዴት እንደ ተቸከሉ! (19) and the mountains, how they are firmly set up;
(20) ወደ ምድርም እንዴ እንደተዘረጋች (አይመለከቱምን?) (20) and the earth, how it is spread out?
(21) አስታውስም፤ አንተ አስታዋሽ ብቻ ነህና፡፡ (21) So remind [O Prophet]; your duty is only to remind;
(22) በእነርሱ ላይ ተሿሚ (አስገዳጅ) አይደለህም፡፡ (22) you are not assigned to compel them.
(23) ግን (ከእውነት) የዞረና የካደ ሰው፤ (23) But whoever turns away and disbelieves,
(24) አላህ ታላቁን ቅጣት ይቀጣዋል፡፡ (24) Allah will inflict upon him the greatest punishment.
(25) መመለሻቸው ወደእኛ ብቻ ነው፡፡ (25) Indeed, to Us is their return,
(26) ከዚያም ምርመራቸው በእኛ ላይ ብቻ ነው፡፡ (26) then it is for Us to call them to account.

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

68 – Al-Qalam

68 – Al-Qalam (1) ነ.(ኑን)፤ በብርእ እምላለሁ በዚያም (መልአኮች) በሚጽፉት፡፡ (1) Nūn. By the pen and what they [the angels] write [in the Records of…

19 Maryam

(1) ከ.ሀ.የ.ዐ.ጸ (ካፍ ሃ ያ ዓይን ሷድ) (1) Kāf Ha Ya ‘Ayn Sād (2) (ይህ) ጌታህ ባሪያውን ዘከሪያን በችሮታው ያወሳበት ነው፡፡ (2) This…

61 – As-Saff

61 – As-Saff (1) በሰማያት ውስጥ ያለው በምድርም ውስጥ ያለው ሁሉ ለአላህ አሞገሠ፡፡ እርሱም አሸናፊው ጥበበኛው ነው፡፡ (1) All that…