Default Image
17, Dec 2023
80 – Abasa

80 – Abasa

(1) ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡(1) He frowned and turned away,
(2) ዕውሩ ስለ መጣው፡፡(2) when the blind man came to him.
(3) ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡(3) How would you know? Perhaps he might be purified,
(4) ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡(4) or he might take heed and benefit from the reminder?
(5) የተብቃቃው ሰውማ፤(5) But he who was indifferent,
(6) አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡(6) you give him your full attention,
(7) ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡(7) although you are not to be blamed if he does not purify himself.
(8) እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤(8) But as for the one who came to you striving [for purification],
(9) እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤(9) and he fears Allah,
(10) አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡(10) you let yourself to be distracted from him.
(11) ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡(11) No indeed; this is a reminder –
(12) የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡(12) so whoever wills may give heed to it –
(13) በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡(13) on venerable pages,
(14) ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡(14) exalted and purified,
(15) በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡(15) [preserved] in the hands of angel-scribes,
(16) የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡(16) honorable and obedient.
(17) ሰው ተረገመ፤ ምን ከሓዲ አደረገው?(17) Woe to man; how ungrateful he is!
(18) (ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)(18) From what did He create him?
(19) ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡(19) He created him from a drop of semen and proportioned him,
(20) ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡(20) then He made the way easy for him;
(21) ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡(21) then He caused him to die and be buried;
(22) ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡(22) then when He wills, He will resurrect him.
(23) በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡(23) Yet he has not fulfilled what He commanded him.
(24) ሰውም ወደ ምግቡ ይመልከት፡፡(24) Let man consider the food he eats:
(25) እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡(25) How We poured down rainwater in torrents,
(26) ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤(26) and caused the soil to split open [for sprouts],
(27) በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤(27) and cause grains to grow in it,
(28) ወይንንም፤ እርጥብ ያበቀልን፤(28) as well as grapes and fodder,
(29) የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤(29) and olive trees and date palms,
(30) ጭፍቆች አትክልቶችንም፤(30) and dense orchards,
(31) ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡(31) and fruits and grass,
(32) ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡(32) as provision for you and your livestock.
(33) አደንቋሪይቱም (መከራ) በመጣች ጊዜ፤(33) But when the Deafening Blast comes,
(34) ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤(34) on that Day everyone will flee from his sibling,
(35) ከናቱም ካባቱም፤(35) and from his mother and father,
(36) ከሚስቱም ከልጁም፤(36) and from his wife and children.
(37) ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ኹነታ አልለው፡፡(37) On that day, everyone will have enough concern of his own.
(38) ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤(38) On that Day, some faces will be bright,
(39) ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው፡፡(39) cheerful and rejoicing;
(40) ፊቶችም በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትቢያ አልለባቸው፤(40) while other faces will be dust-stained,
(41) ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤(41) covered in darkness.
(42) እነዚያ እነሱ ከሓዲዎቹ አመጸኞቹ ናቸው፡፡(42) Such are the disbelievers, the wicked.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

94 – Ash-Sharh

94 – Ash-Sharh (1) ልብህን ለአንተ አላሰፋንልህምን? (አስፍተንልሃል)፡፡ (1) Have We not reassured your heart for you [O Prophet], (2) ሸክምህንም ካንተ…

90 – Al-Balad

90 – Al-Balad (1) በዚህ አገር (በመካ) እምላለሁ፡፡ (1) I do swear by this city [of Makkah] – (2) አንተ በዚህ አገር ሰፋሪ ስትኾን፡፡…

58 – Al-Mujaadila

58 – Al-Mujaadila (1) አላህ የዚያችን በባሏ (ነገር) የምተከራከርህንና ወደ አላህ የምታሰሙተውን (ሴት) ቃል በእርግጥ ሰማ፡፡ አላህም (በንግግር) መመላለሳችሁን ይሰማል፡፡ አላህ ሰሚ ተመልካች ነውና፡፡ (1) Indeed,…