Default Image
10, Dec 2023
26 – Ash-Shu’araa

26 – Ash-Shu’araa

(1) ጠ.ሰ.መ. (ጧ ሲን ሚም)፡፡(1) Tā sīn mīm.
(2) ይህች ግልጽ ከኾነው መጽሐፍ አንቀጾች ናት፡፡(2) These are the verses of the clear Book.
(3) አማኞች ባለመኾናቸው፤ (በቁጭት) ነፍስህን ገዳይ መኾን ይፈራልሃል፡፡(3) Perhaps you will grieve yourself to death because they do not believe.
(4) ብንሻ በእነሱ ላይ ከሰማይ ተዓምረን እናወርድና አንገቶቻቸው (መሪዎቻቸው) ለእርሷ ተዋራጆች ይኾናሉ፡፡(4) If We willed, We could send down upon them a sign from the heaven, at which their necks would stay bowed in humility.
(5) ከአልረሕማንም ዘንድ ኣዲስ የተወረደ ቁርኣን አይመጣላቸውም፤ ከእርሱ የሚሸሹ ቢኾኑ እንጂ፡፡(5) No new reminder comes to them from the Most Compassionate except that they turn away from it.
(6) በእርግጥም አስተባበሉ፡፡ የዚያም በእርሱ ይሳለቁበት የነበሩት ወሬዎች (ፍጻሜ) ይመጣባቸዋል፡፡(6) They have rejected [the Truth], soon there will come to them the consequences of their ridicule.
(7) ወደ ምድርም በውስጧ ከመልካም (በቃይ) ጎሳ ሁሉ ብዙን እንዳበቀልን አላዩምን፡፡(7) Do they not see the earth, how many fine kinds of plants We grow in it?
(8) በዚህ አስደናቂ ምልክት አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡(8) Indeed, there is a sign in this, yet most of them will not believe.
(9) ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊ አዛኝ ነው፡፡(9) Your Lord is indeed the All-Mighty, the Most Merciful.
(10) ጌታህም ሙሳን «ወደ በደለኞቹ ሕዝቦች ኺድ» በማለት በጠራው ጊዜ (አስታውስ)፡፡(10) And [remember] when your Lord called out to Moses, “Go to the wrongdoing people –
(11) «ወደ ፈርዖን ሕዝቦች (ኺድ) አላህን አይፈሩምን» (አለው)፡፡(11) the people of Pharaoh; will they not fear [the punishment of] Allah?”
(12) (ሙሳም) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔ ሊያስተባብሉኝ እፈራለሁ፡፡(12) He said, “My Lord, I fear that they may reject me,
(13) «ልቤም ይጠብባል፡፡ ምላሴም አይፈታም፡፡ ስለዚህ ወደ ሃሩን ላክ፡፡(13) and I will feel distressed and my tongue will not be fluent, so send Aaron along [to help me].
(14) «ለእነርሱም በእኔ ላይ (የደም) ወንጀል አልለ፡፡ ስለዚህ እንዳይገድሉኝ እፈራለሁ፡፡»(14) Moreover, they have a charge against me, so I fear they may kill me.”
(15) (አላህ) አለ «ተው! (አይነኩህም)፡፡ በተዓምራቶቻችንም ኺዱ፡፡ እኛ ከእናንተ ጋር ሰሚዎች ነንና፡፡(15) Allah said, “Certainly not! Go, both of you, with Our signs; We are with you, listening.
(16) «ወደ ፈርዖንም ኺዱ፡፡ በሉትም፡- እኛ የዓለማት ጌታ መልክተኞች ነን፡፡(16) Go to Pharaoh and say, ‘We are the messengers from the Lord of the worlds,
(17) «የእስራኤልን ልጆች ከእኛ ጋር ልቀቅ፡፡»(17) that you let the Children of Israel go with us.’”
(18) (ፈርዖንም) አለ «ልጅ ኾነህ በእኛ ውስጥ አላሳደግንህምን በእኛ ውስጥም ከዕድሜህ ብዙ ዓመታትን አልተቀመጥክምን(18) Pharaoh said, “Did we not bring you up as a child among us, and you stayed with us several years of your life?
(19) «ያችንም የሠራሃትን ሥራህን አልሠራህምን አንተም ከውለታ ቢሶቹ ነህ» (አለ)፡፡(19) Yet you did what you did, and you are extremely ungrateful.”
(20) (ሙሳም) አለ «ያን ጊዜ እኔም ከተሳሳቱት ኾኜ ሠራኋት፡፡(20) He said, “I did it when I had no guidance.
(21) «በፈራኋችሁም ጊዜ ከእንናተ ሸሸሁ፡፡ ጌታየም ለእኔ ጥበብን ሰጠኝ፡፡ ከመልክተኞቹም አደረገኝ፡፡(21) So I fled from you in fear. Then my Lord gave me wisdom and made me one of the messengers.
(22) «ይህችም የእስራኤልን ልጆች ባሪያ በማድረግህ በእኔ ላይ የምትመጻደቅባት ጸጋ ነት፡፡»(22) Is this a favor that you remind me with, that you have enslaved the Children of Israel?
(23) ፈርዖን አለ «(ላከኝ የምትለው) የዓለማትም ጌታ ምንድነው»(23) Pharaoh said, “What is ‘the Lord of the worlds’?”
(24) (ሙሳ) «የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምታረጋግጡ ብትኾኑ (ነገሩ ይህ ነው)፤» አለው፡፡(24) Moses said, “The Lord of the heavens and earth and all that is between them, if only you had sure faith.”
(25) (ፈርዖንም) በዙሪያው ላሉት ሰዎች «አትሰሙምን» አለ፡፡(25) Pharaoh said to those around him, “Did you hear [what he just said]?”
(26) (ሙሳ) «ጌታችሁና የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው» አለው፡፡(26) Moses said, “Your Lord and the Lord of your forefathers.”
(27) (ፈርዖን)(27) Pharaoh said, “Your messenger who has been sent to you is truly insane!”
(28) (ሙሳ) «የምሥራቅና የምዕራብ በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ ታውቁ እንደኾናችሁ (እመኑበት)» አለው፡፡(28) Moses said, “Lord of the east and west and all that is between them, if only you had sense!”
(29) (ፈርዖን) «ከእኔ ሌላ አምላክን ብትይዝ በውነቱ ከእስረኞቹ አደርግሃለሁ» አለ፡፡(29) Pharaoh said, “If you take any god other than me, I will throw you into prison.”
(30) (ሙሳ) «በግልጽ አስረጅ ብመጣህም እንኳ» አለው፡፡(30) Moses said, “What if I bring you a clear proof?”
(31) «እንግዲያውስ ከእውነተኞች እንደኾንክ (አስረጁን) አምጣው» አለ፡፡(31) Pharaoh said, “Bring it then, if you are truthful!”
(32) በትሩንም ጣለ፡፡ እርሷም ወዲያውኑ ግልጽ እባብ ኾነች፡፡(32) So he threw down his staff, and suddenly it was a real serpent.
(33) እጁንም አወጣ፡፡ ወዲያውም እርሷ ለተመልካቾች (የምታበራ) ነጭ ኾነች፡፡(33) And he drew out his hand, and it was glowing white to the beholders.
(34) (ፈርዖን) በዙሪያው ላሉት መማክርት «ይህ በእርግጥ ዐዋቂ ድግምተኛ ነው» አለ፡፡(34) Pharaoh said to the chiefs around him, “This is indeed a learned magician!
(35) «ከምድራችሁ በድግምቱ ሊያወጣችሁ ይፈልጋልና ምንን ታዛላችሁ» (አላቸው)፡፡(35) He wants to drive you out of your land with his magic. What do you suggest?”
(36) አሉት «እርሱን ወንድሙንም አቆይና በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን ላክ፡፡(36) They said, “Let him and his brother wait and dispatch heralds to the cities
(37) «በጣም ዐዋቂ ድግምተኞችን ሁሉ ያመጡልሃልና፡፡»(37) to bring you every learned magician.”
(38) ድግምተኞቹም በታወቀ ቀን ቀጠሮ ተሰበሰቡ፡፡(38) So the magicians were assembled at an appointed time on a known day.
(39) ለሰዎቹም «እናንተ ተሰብስባችኋልን» ተባለ፡፡(39) And it was said to the people, “Will you join the gathering,
(40) «ድግምተኞቹን እነሱ አሸናፊዎች ቢኾኑ እንከተል ዘንድ» (ተባለ)፡፡(40) so that we may follow the magicians if they are victorious?”
(41) «ድግምተኞቹም በመጡ ጊዜ ለፈርዖን እኛ አሸናፊዎች ብንሆን ለእኛ በእርግጥ ዋጋ አለን» አሉት፡፡(41) When the magicians came, they said to Pharaoh, “Will there be a reward for us if we are victorious?”
(42) «አዎን፤ እናንተም ያን ጊዜ ከባለሟሎቹ ትኾናላችሁ» አላቸው፡፡(42) He said, “Yes, and then you will surely be of those who are close to me.”
(43) ሙሳ «ለእነርሱ እናንተ የምትጥሉትን ጣሉ» አላቸው፡፡(43) Moses said to them, “Throw whatever you wish to throw.”
(44) ገመዶቻቸውንና በትሮቻቸውንም ጣሉ፡፡ «በፈርዖንም ክብር ይኹንብን፡፡ እኛ በእርግጥ አሸናፊዎቹ እኛ ነን» አሉ፡፡(44) So they threw their ropes and staffs, and said, “By the glory of Pharaoh, it is we who will be the victorious!”
(45) ሙሳም በትሩን ጣለ፡፡ ወዲያውም እርሷ የሚያስመስሉትን ሁሉ ትውጣለች፡፡(45) Then Moses threw his staff, and at once it swallowed up all objects of their illusion.
(46) ድግምተኞቹም ሰጋጆች ኾነው ወደቁ፡፡(46) So the magicians fell down in prostration.
(47) (እነሱም) አሉ «በዓለማት ጌታ አመንን፡፡(47) They said, “We believe in the Lord of the worlds,
(48) «በሙሳና በሃሩን ጌታ፡፡»(48) the Lord of Moses and Aaron.”
(49) (ፈርዖንም) «ለእናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት ለእርሱ አመናችሁን እርሱ ያ ድግምትን ያስተማራችሁ ታላቃችሁ ነው፡፡ ወደፊትም (የሚያገኛችሁን) በእርግጥ ታውቃላችሁ፡፡ እጆቻችሁንና እግሮቻችሁን (ቀኝና ግራን) በማናጋት እቆረርጣለሁ፡፡ ሁላችሁንም እሰቅላችኋለሁም» አለ፡፡(49) Pharaoh said, “How dare you believe in him before I give you permission. Indeed, he is your master who taught you magic, but you will soon come to know. I will surely cut off your hands and feet on opposite sides, then I will crucify you all.”
(50) (እነርሱም) አሉ «ጉዳት የለብንም፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ተመላሾች ነን፡፡(50) They said, “No harm; we will surely return to our Lord.
(51) «እኛ የምእምናን መጀመሪያ በመኾናችን ጌታችን ኀጢአቶቻችንን ለእኛ ሊምር እንከጅላለን፡፡»(51) We hope that our Lord will forgive us our sins, as we are the first of the believers.”
(52) ወደ ሙሳም «ባሮቼን ይዘህ ሌሊት ኺድ፡፡ እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና» ስንል ላክን፡፡(52) We inspired Moses, “Leave with My slaves by night; you will surely be pursued.”
(53) ፈርዖንም በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን (እንዲህ ሲል) ላከ፡፡(53) So Pharaoh sent heralds to the cities,
(54) «እነዚህ ጥቂቶች ጭፈሮች ናቸው፡፡(54) saying, “These are but a small band,
(55) «እነርሱም ለእኛ አስቆጪዎች ናቸው፡፡(55) and they have enraged us,
(56) «እኛም ብዙዎች ጥንቁቆች ነን፤» (አለ)፡፡(56) but we are all well-prepared.”
(57) አወጣናቸውም፡፡ ከአትክልቶችና ከምንጮች፡፡(57) Thus did We drive them out of their gardens and springs,
(58) ከድልቦችም ከመልካም መቀመጫዎችም፡፡(58) and their treasures and splendid dwellings.
(59) እንደዚሁ ለእስራኤል ልጆች አወረስናትም፡፡(59) So it was; and We made the Children of Israel to inherit them.
(60) ፀሐይዋ ስትወጣም ተከተሉዋቸው፡፡(60) They pursued them at sunrise.
(61) ሁለቱ ጭፍሮችም በተያዩ ጊዜ የሙሳ ጓዶች «እኛ(የፈርዖን ሰዎች) የሚደርሱብን ነን» አሉ፡፡(61) When the two groups saw each other, the companions of Moses said, “We are surely overtaken!”
(62) (ሙሳ) «ተዉዉ! ጌታዬ ከእኔ ጋር ነው፡፡ በእርግጥ ይመራኛል» አለ፡፡(62) Moses said, “Certainly not! My Lord is with me; He will guide me.”
(63) ወደ ሙሳም «ባሕሩን በበትርህ ምታው» ስንል ላክንበት፡፡ (መታውና) ተከፈለም፡፡ ክፍሉም ሁሉ እንደ ታላቅ ጋራ ኾነ፡፡(63) Then We inspired Moses, “Strike the sea with your staff,” so it parted, each part became like a huge mountain.
(64) እዚያም ዘንድ ሌሎችን አቀረብን፡፡(64) Then We brought the others [pursuers] close to that place,
(65) ሙሳንም ከእርሱ ገር ያሉትንም ሰዎች ሁሉንም አዳን፡፡(65) and We saved Moses and all those who were with him,
(66) ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡(66) then We drowned the others.
(67) በዚህ ውስጥ ታላቅ ታምር አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡(67) Indeed, there is a sign in this, yet most of them would not believe.
(68) ጌታህም እርሱ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡(68) Indeed, your Lord is the All-Mighty, the Most Merciful.
(69) በእነሱም (በሕዝቦችህ) ላይ የኢብራሂምን ወሬ አንብብላቸው፡፡(69) Relate to them the story of Abraham,
(70) ለአባቱና ለሕዝቦቹ «ምንን ትግገዛላችሁ» ባለ ጊዜ፡፡(70) when he said to his father and his people, “What do you worship?”
(71) «ጣዖታትን እንገዛለን፤ እርሷንም በመገዛት ላይ እንቆያለን» አሉ፡፡(71) They said, “We worship idols and remain devoted to them.”
(72) (እርሱም) አለ «በጠራችኋቸው ጊዜ ይሰሟችኋልን(72) He said, “Do they hear you when you call upon them?
(73) «ወይስ ይጠቅሟችኋልን ወይስ ይጎዷችኋልን»(73) Or can they benefit or harm you?”
(74) «የለም! አባቶቻችን እንደዚሁ ሲሠሩ አገኘን» አሉት፡፡(74) They said, “No, but this is what we found our forefathers doing.”
(75) «ትግገዙት የነበራችሁትን አስተዋላችሁን(75) He said, “Do you see what you have been worshiping,
(76) «እናንተም የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁም (የተግገዛችሁትን)፡፡»(76) you and your ancestors?
(77) «እነሱም (ጣዖቶቹ) ለእኔ ጠላቶች ናቸው፡፡ ግን የዓለማት ጌታ ሲቀር (እርሱ ወዳጄ ነው)፡፡(77) Indeed, they are my enemies, except the Lord of the worlds,
(78) «(እርሱ) ያ የፈጠረኝ ነው፡፡ እርሱም ይመራኛል፡፡(78) Who created me, so He guides me;
(79) «ያም እርሱ የሚያበላኝና የሚያጠጣኝ ነው፡፡(79) and it is He Who provides me with food and drink;
(80) «በታመምኩም ጊዜ እርሱ ያሽረኛል፡፡(80) and when I am ill He heals me;
(81) «ያም የሚገድለኝ ከዚያም ሕያው የሚያደርገኝ ነው፡፡(81) and He will cause me to die then bring me back to life;
(82) ያም በፍርዱ ቀን ኀጢአቴን ለእኔ ሊምር የምከጅለው ነው፡፡(82) and I hope that He will forgive me my sins on the Day of Judgment.”
(83) ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ስጠኝ! በደጋጎቹም ሰዎች አስጠጋኝ፡፡(83) “My Lord, grant me knowledge, and join me with the righteous,
(84) በኋለኞቹም ሕዝቦች ውስጥ ለእኔ መልካም ዝናን አድርግልኝ፡፡(84) and grant me an honorable mention among the later generations,
(85) የጸጋይቱን ገነት ከሚወርሱትም አድርገኝ፡፡(85) and make me of those who will inherit the Garden of Bliss;
(86) ለአባቴም ማር፡፡ እርሱ ከተሳሳቱት ነበረና፡፡(86) and forgive my father, for he is one of those who have gone astray;
(87) በሚቀሰቀሱበት ቀንም አታዋርደኝ፡፡(87) and do not disgrace me on the Day when all will be resurrected –
(88) ገንዘብም ልጆችም በማይጠቅሙበት ቀን፡፡(88) the Day when neither wealth nor children will be of any avail,
(89) ወደ አላህ በንጹህ ልብ የመጣ ሰው ቢኾን እንጅ፡፡»(89) except the one who comes to Allah with a sound heart.”
(90) ገነትም ለፈሪዎች በምትቀረብበት (ቀን)፡፡(90) Paradise will be brought near to the righteous,
(91) ገሀነምም ለጠመሞች በምትገለጽበት (ቀን)፡፡(91) and Hellfire will be uncovered to those who went astray,
(92) ለእነሱም በሚባል ቀን «ትግገዟቸው የነበራችሁት የት ናቸው»(92) and they will be told, “Where are those whom you used to worship
(93) «ከአላህ ሌላ ሲኾኑ ይረዱዋችኋልን ወይስ (ለራሳቸው) ይርረዳሉን»(93) other than Allah? Can they help you or even help themselves?”
(94) በውስጧም እነሱና ጠማሞቹ በፊቶቻቸው ተጥለው ይንከባለላሉ፡፡(94) Then they will be hurled into Hell one upon another, along with those who led them astray,
(95) የሰይጣንም ሰራዊቶች መላውም (ይጣላሉ)፡፡(95) and the followers of Iblīs, all together.
(96) እነርሱም በእርሷ ውስጥ የሚከራከሩ ኾነው ይላሉ፡-(96) There the deviants will say while quarreling with their false deities,
(97) በአላህ እንምላለን፤ እኛ በግልጽ መሳሳት ውስጥ ነበርን፡፡(97) “By Allah, we were clearly misguided,
(98) (ጣዖቶቹን) በዓለማት ጌታ ባስተካከልናችሁ ጊዜ፡፡(98) when we deemed you equal to the Lord of the worlds.
(99) አመጸኞቹም እንጅ ሌላ አላሳሳተንም፡፡(99) None led us astray except the wicked.
(100) ከአማላጆችም ለእኛ ምንም የለንም፡፡(100) Now we neither have any intercessors,
(101) አዛኝ ወዳጂም (የለንም)፡፡(101) nor a close friend.
(102) ለእኛም አንዲት ጊዜ መመለስ በኖረችንና ከአማኞቹ በኾን እንመኛለን (ይላሉ)፡፡(102) If only we had a chance to return, we would be among the believers.”
(103) በዚህ ውስጥ አስደናቂ ግሳጼ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡(103) Indeed, there is a sign in this, yet most of them would not believe.
(104) ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡(104) Your Lord is surely the All-Mighty, the Most Merciful.
(105) የኑሕ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባበሉ፡፡(105) The people of Noah rejected the messengers
(106) ወንድማቸው ኑሕ ለእነሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን(106) when their brother Noah said to them, “Do you not fear Allah?
(107) «እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡(107) I am a trustworthy messenger to you,
(108) «አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡(108) so fear Allah, and obey me.
(109) «በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡(109) I seek of you no reward for this; my reward is only with the Lord of the worlds;
(110) «አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡»(110) so fear Allah, and obey me.”
(111) (እነርሱም) «ወራዶቹ የተከተሉህ ኾነህ ለአንተ እናምናለን» አሉት፡፡(111) They said, “Shall we believe in you when you are followed by the lowest people?”
(112) (እርሱም) አላቸው «ይሠሩት በነበሩት ነገር ምን ዕውቀት አለኝ፡፡(112) He said, “What knowledge do I have of what they do?
(113) «ምርመራቸው በጌታዬ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ ብታውቁ ኖሮ (ይህንን ትርረዱ ነበር)፡፡(113) Their reckoning is only with my Lord, if you realize!
(114) «እኔም አማኞችን አባራሪ አይደለሁም፡፡(114) I am not going to drive the believers away.
(115) «እኔ ግልጽ አስፈራሪ እንጅ ሌላ አይደለሁም፡፡»(115) I am only a clear warner.”
(116) «ኑሕ ሆይ! (ከምትለው) ባትከለከል በእርግጥ ከሚወገሩት ትኾናለህ» አሉት፡፡(116) They said, “O Noah, if you do not desist, you will certainly be stoned.”
(117) (እርሱም) አለ «ጌታዬ ሆይ! ሕዝቦቼ አስተባበሉኝ፡፡(117) He said, “My Lord, my people have rejected me.
(118) «በእኔና በእነርሱም መካከል (ተገቢ) ፍርድን ፍረድ፡፡ አድነኝም፡፡ ከእኔ ጋር ያሉትንም ምእምናን፡፡»(118) So judge between me and them decisively, and save me and the believers who are with me.”
(119) እርሱንም ከእርሱ ጋር ያለውንም ሁሉ በተመላው መርከብ ውስጥ አዳን፡፡(119) So We saved him and those who were with him in the fully laden Ark.
(120) ከዚያም በኋላ ቀሪዎቹን አሰጠምን፡፡(120) Then We drowned thereafter all the rest.
(121) በዚህ ውስጥ ታላቅ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡(121) Indeed, there is a sign in this, yet most of them would not believe.
(122) ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡(122) Indeed, your Lord is the All-Mighty, the Most Merciful.
(123) ዓድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡(123) The people of ‘Ād rejected the messengers
(124) ወንድማቸው ሁድ ለነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን(124) when their brother Hūd said to them, “Will you not fear Allah?
(125) «እኔ ለናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡(125) I am a trustworthy messenger to you,
(126) «አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡(126) so fear Allah, and obey me.
(127) «በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡(127) I do not ask you for any reward for this; my reward is only with the Lord of the worlds.
(128) «የምትጫወቱ ኾናችሁ በከፍተኛ ስፍራ ሁሉ ላይ ምልክትን ትገነባላችሁን(128) Do you build a landmark on every high place for no purpose?
(129) «የውሃ ማጠራቀሚያዎችንና ሕንፃዎችንም ዘላለም መኖርን የምትከጅሉ ኾናችሁ ትሠራላችሁን(129) And do you construct for yourselves palaces, hoping that you will live forever?
(130) «በቀጣችሁም ጊዜ ጨካኞች ኾናችሁ ትቀጣላችሁን(130) And when you attack [others], do you attack ruthlessly?
(131) «አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡(131) So fear Allah, and obey me.
(132) «ያንንም በምታውቁት (ጸጋ) ያጣቀማችሁን ፍሩ፡፡(132) And fear the One Who has provided you with everything you know:
(133) «በእንስሳዎችና በልጆች ያጣቀማችሁን፡፡(133) Who provided you with livestock and children,
(134) «በአትክልቶችና በምንጮችም፡፡(134) and with gardens and springs.
(135) «እኔ በእናንተ ላይ የታላቅን ቀን ቅጣት እፈራለሁና፡፡»(135) I fear for you the punishment of a momentous day.”
(136) (እነርሱም) አሉ «ብትገስጽም ወይም ከገሳጮቹ ባትኾንም በእኛ ላይ እኩል ነው፤ (ያለንበትን አንለቅም)፡፡(136) They said, “It is the same to us whether you admonish us or not.
(137) «ይህ የፊተኞቹ ሰዎች ፀባይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡(137) This is nothing but the custom of the former people,
(138) «እኛም የምንቅቀጣ አይደለንም» (አሉ)፡፡(138) and we will never be punished.”
(139) አስተባበሉትም፡፡ አጠፋናቸውም፡፡ በዚህም ውስጥ እርግጠኛ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡(139) Thus they rejected him, so We destroyed them. Indeed, there is a sign in this, yet most of them would not believe,
(140) ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡(140) Your Lord is indeed the All-Mighty, the Most Merciful.
(141) ሰሙድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡(141) The people of Thamūd rejected the messengers
(142) ወንድማቸው ሷሊህ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን(142) when their brother Sālih said to them, “Will you not fear Allah?
(143) «እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡(143) I am a trustworthy messenger to you,
(144) «አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡(144) so fear Allah, and obey me.
(145) «በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡(145) I do not ask you for any reward for this; my reward is only with the Lord of the worlds.
(146) «በዚያ እዚህ ባለው (ጸጋ) ውስጥ የረካችሁ ኾናችሁ ትተዋላችሁን(146) Will you be left secure in whatever you have here,
(147) «በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ፡፡(147) in gardens and springs,
(148) «በአዝመራዎችም ፍሬዋ የበሰለ በኾነች ዘንባባም፤ (ውስጥ ትተዋላችሁን)(148) and in fields of crops and date-palms laden with tender fruit,
(149) «ብልሆች ኾናችሁ ከጋራዎች ቤቶችንም ትጠርባላችሁ፡፡(149) carving out houses in the mountains with great skill?
(150) «አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡(150) So fear Allah, and obey me.
(151) «የወሰን አላፊዎችንም ትዕዛዝ አትከተሉ፡፡(151) And do not obey the command of the transgressors,
(152) «የእነዚያን በምድር ላይ የሚያጠፉትንና የማያበጁትን፡፡»(152) those who spread corruption in the land and never do what is right.”
(153) (እነሱም) አሉ «አንተ በብዙ ከተደገመባቸው ሰዎች ብቻ ነህ፡፡(153) They said, “You are but one of those who are bewitched!
(154) «አንተ ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ ከእውነተኞቹም እንደኾንክ ተዓምርን አምጣ፡፡»(154) You are but a human like us, so bring a sign if you are one of the truthful.”
(155) (እርሱም) አለ «ይህች ግመል ናት፡፡ ለእርሷ የመጠጥ ፋንታ አላት፡፡ ለእናንተም የታወቀ ቀን ፋንታ አላችሁ፡፡(155) Sālih said, “This is a she-camel; she will have her share of water and you will have yours, each on a specified day.
(156) «በክፉም አትንኳት፡፡ የታላቅ ቀን ቅጣት ይይዛችኋልና፡፡»(156) Do not touch her with harm, or you will be seized by the punishment of a horrible day.”
(157) ወጓትም፡፡ ወዲያውም ተጸጻቾች ኾነው አነጉ፡፡(157) But they hamstrung her, then they became regretful,
(158) ቅጣቱም ያዛቸው፡፡ በዚህም ውስጥ ግሳፄ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡(158) So the punishment seized them. Indeed, there is a sign in this, yet most of them would not believe.
(159) ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡(159) Your Lord is indeed the All-Mighty, the Most Merciful.
(160) የሉጥ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባባሉ፡፡(160) The people of Lot rejected the messengers,
(161) ወንድማቸው ሉጥ ለእነርሱ ባለ ጊዜ «አትጠነቀቁምን(161) when their brother Lot said to them, “Will you not fear Allah?
(162) «እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡(162) I am a trustworthy messenger to you,
(163) «አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡(163) so fear Allah, and obey me.
(164) «በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡(164) I do not ask you for any reward for this; my reward is only with the Lord of the worlds.
(165) «ከዓለማት ሰዎች ወንዶችን ትመጣላችሁን(165) Do you approach males with lust among all people,
(166) «ከሚስቶቻችሁም ጌታችሁ ለናንተ የፈጠረላችሁን ትተዋላችሁን በእውነቱ እናንተ ወሰን አላፊዎች ሕዝቦ ናችሁ፡፡»(166) leaving the wives whom your Lord has created for you? You are but a transgressing people.”
(167) (እነርሱም) አሉ «ሉጥ ሆይ! ባትከለከል በእርግጥ (ከአገር) ከሚወጡት ትኾናለህ፡፡»(167) They said, “O Lot, If you do not desist, you will surely be expelled.”
(168) (እርሱም) አለ «እኔ ሥራችሁን ከሚጠሉት ሰዎች ነኝ፡፡(168) Lot said, “I utterly abhor your practice.
(169) «ጌታዬ ሆይ! እኔንም ቤተሰቦቼንም ከሚሠሩት ሥራ (ቅጣት) አድነን፡፡»(169) My Lord, save me and my family from [the consequences of] what they do.”
(170) እርሱንም ቤተሰቦቹንም በጠቅላላ አዳንናቸው፡፡(170) So We saved him and all his family,
(171) በቀሪዎቹ ውስጥ የኾነች አሮጊት ብቻ ስትቀር (እርሷ ጠፋች)፡፡(171) except an old woman who was among those who remained behind.
(172) ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡(172) Then We destroyed the rest,
(173) በእነሱም ላይ (የድንጋይን) ዝናምን አዘነምንባቸው፡፡ የተስፈራሪዎቹም ዝናም (ምንኛ) ከፋ፡፡(173) and We poured down upon them a rain [of stones]. How terrible was the rain of those who were warned!
(174) በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡(174) Indeed, there is a sign in this, yet most of them would not believe.
(175) ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡(175) Your Lord is indeed the All-Mighty, the Most Merciful.
(176) የአይከት ሰዎች መልክተኞችን አስተባበሉ፤(176) The people of the Forest rejected the messengers.
(177) ሹዕይብ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን(177) When Shu‘ayb said to them, “Will you not fear Allah?
(178) «እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡(178) I am a trustworthy messenger to you,
(179) «አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡(179) so fear Allah, and obey me.
(180) «በርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡(180) I do not ask you for any reward for this; my reward is only with the Lord of the worlds.
(181) «ስፍርን ሙሉ፡፡ ከአጉዳዮቹም አትኹኑ፡፡(181) Give full measure and do not be of those who defraud others,
(182) «በትክክለኛ ሚዛንም መዝኑ፡፡(182) and weigh with accurate scales,
(183) «ሰዎችንም ነገሮቻቸውን አታጉድሉባቸው፡፡ በምድርም ላይ አጥፊዎች ኾናችሁ አታበላሹ፡፡(183) and do not defraud people of their goods, nor go about in the land spreading corruption.
(184) «ያንንም የፈጠራችሁን የቀድሞዎቹንም ፍጡሮች (የፈጠረውን) ፍሩ፡፡»(184) And fear the One Who created you and the former peoples.”
(185) አሉ «አንተ በብዛት ከተደገመባቸው ሰዎች ነህ፡፡(185) They said, “You are truly bewitched!
(186) «አንተም ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ እነሆ ከውሸታሞች ነህ ብለን እንጠረጥርሃለን፡፡(186) You are only a human being like us, and we think you are nothing but a liar.
(187) «ከእውነተኞቹም እንደኾንክ በእኛ ላይ ከሰማይ ቁራጭን ጣልብን፡፡»(187) So cause pieces of the sky to fall upon us, if you are of the truthful.”
(188) «ጌታዬ የምትሠሩትን ሁሉ ዐዋቂ ነው፤» አላቸው፡፡(188) Shu‘ayb said, “My Lord knows best whatever you do.”
(189) አስተባበሉትም፡፡ የጥላይቷ ቀን ቅጣትም ያዛቸው፡፡ እርሱ የከባድ ቀን ቅጣት ነበርና፡፡(189) Thus they rejected him, so they were seized by the punishment of the cloudy day; it was the punishment of a horrible day.
(190) በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእምናን አልነበሩም፡፡(190) Indeed, there is a sign in this, yet most of them would not believe.
(191) ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡(191) Your Lord is indeed the All-Mighty, the Most Merciful.
(192) እርሱም (ቁርኣን) በእርግጥ ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡(192) This is indeed a revelation from the Lord of the worlds,
(193) እርሱን ታማኙ መንፈስ (ጂብሪል) አወረደው፤(193) which the Trustworthy Spirit [Gabriel] has brought down
(194) ከአስፈራሪዎቹ (ነቢያት) ትኾን ዘንድ በልብህ ላይ (አወረደው)፡፡(194) to your heart [O Prophet] so that you may be one of the warners,
(195) ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ፡፡(195) in a clear Arabic language.
(196) እርሱም (ቁርኣን) በቀድሞዎቹ መጻሐፍት ውስጥ (የተወሳ ነው)፡፡(196) And it was indeed [mentioned] in the scriptures of the former peoples.
(197) የእስራኤል ልጆች ሊቃውንት የሚያውቁት መኾኑ ለእነርሱ (ለመካ ከሓዲዎች) ምልክት አይኾናቸውምን(197) Was it not a proof for them that the learned men of the Children of Israel recognized it [to be true]?
(198) ከአዕጀሞች ባንዱ ላይ ባወረድነውም ኖሮ፤(198) If We had sent it down to any of the non-Arabs,
(199) በእነርሱ ላይ ባነበበውም በእርሱ አማኞች አይኾኑም ነበር፡፡(199) and he had recited it to them, still they would not have believed in it.
(200) እንደዚሁ (ማስተባበልን) በተንኮለኞች ልቦች ውስጥ አስገባነው፡፡(200) This is how We made it [disbelief] enter the hearts of the wicked.
(201) አሳማሚ ቅጣትን እስከሚያዩ ድረስ በእርሱ አያምኑም፡፡(201) They will not believe in it until they see the painful punishment,
(202) እነርሱ የማያውቁ ሲኾኑ (ቅጣቱ) ድንገት እስከሚመጣባቸውም ድረስ (አያምኑም)፡፡(202) which will come upon them suddenly when they least expect it.
(203) (በመጣባቸው ጊዜ) «እኛ የምንቆይ ነን» እስከሚሉም (አያምኑም)፡፡(203) They will then say, “Can we be granted some respite?”
(204) በቅጣታችን ያቻኩላሉን(204) Do they really seek to hasten Our punishment?
(205) አየህን ብዙ ዓመታትን ብናጣቅማቸው፤(205) Tell me [O Prophet] if We give them a life of ease for years,
(206) ከዚያም ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ቢመጣባቸው፤(206) then there came to them what they were warned of,
(207) ይጣቀሙበት የነበሩት ሁሉ ከእነሱ ምንም አያብቃቃቸውም፡፡(207) what would avail them the life of ease that they were given?
(208) አንዲትንም ከተማ ለእርሷ አስፈራሪዎች ያሏት (እና ያስተባበለች) ኾና እንጅ አላጠፋንም፡፡(208) We never destroyed any town without sending them warners,
(209) (ይህች) ግሳፄ ናት፡፡ በዳዮችም አልነበርንም፡፡(209) to admonish them, for We are never unjust.
(210) ሰይጣናትም እርሱን (ቁርኣንን) አላወረዱትም፡፡(210) This [Qur’an] is not sent down by the devils,
(211) ለእነርሱም አይገባቸውም፤ አይችሉምም፡፡(211) it is not for them to do this, nor is it within their capability,
(212) እነርሱ (የመላእክትን ንግግር) ከመስማት ተከለከሉ ናቸው፡፡(212) for they are strictly barred from overhearing it.
(213) ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አትግገዛ፤ ከሚቀጡት ትኾናለህና፡፡(213) So do not call upon any other god besides Allah, lest you become of those who will be punished.
(214) ቅርቦች ዘመዶችህንም አስጠንቅቅ፡፡(214) And warn [starting with] the nearest kinsfolk,
(215) ከምእምናንም ለተከተሉህ ሰዎች ክንፍህን ዝቅ አድርግ፤ (ልዝብ ኹን)፡፡(215) and lower your wing [in kindness] to the believers who follow you.
(216) «እንቢ» ቢሉህም «እኔ ከምትሠሩት ንጹሕ ነኝ» በላቸው፡፡(216) But if they disobey you, say, “I disown what you do.”
(217) አሸናፊ አዛኝ በኾነው (ጌታህ) ላይም ተጠጋ፡፡(217) And put your trust in the All-Mighty, the Most Merciful,
(218) በዚያ ለሶላት በምትቆም ጊዜ በሚያይህ፡፡(218) Who sees you when you stand up [for prayer],
(219) በሰጋጆች ውስጥ መዘዋወርህንም (በሚያየው ጌታህ ላይ ተጠጋ)፡፡(219) and your movements among those who prostrate.
(220) እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡(220) Indeed, He is the All-Hearing, the All-Knowing.
(221) ሰይጣናት በማን ላይ እንደሚወርዱ ልንገራችሁን(221) Shall I inform you upon who the devils descend?
(222) በውሸታም ኀጢአተኛ ሁሉ ላይ ይወርዳሉ፡፡(222) They descend upon every sinful liar,
(223) የሰሙትን (ወደ ጠንቋዮች) ይጥላሉ፡፡ አብዛኞቻቸውም ውሸታሞች ናቸው፡፡(223) who whisper hearsay in the ears, but most of them are liars.
(224) ባለ ቅኔዎችንም ጠማማዎቹ ይከተሉዋቸዋል፡፡(224) As for poets, they are followed by the deviants.
(225) እነርሱ በ(ንግግር) ሸለቆ ሁሉ የሚዋልሉ መኾናቸውን አታይምን(225) Do you not see that they wander aimlessly in every valley,
(226) እነሱም የማይሠሩትን ነገር የሚናገሩ መኾናቸውን (አታይምን)፤(226) and that they say what they do not do?
(227) እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችን የሠሩ አላህንም በብዛት ያወሱ ከተበደሉም በኋላ (በቅኔ) የተከላከሉ ሲቀሩ፤ (እነርሱ አይወቀሱም)፡፡ እነዚያም የበደሉ (ከሞቱ በኋላ) እንዴት ያለን መመለስ እንደሚመለሱ በእርግጥ ያውቃሉ፡፡(227) Except those who believe, do righteous deeds, remember Allah much and defend themselves after being wronged. The wrongdoers will come to know what end awaits them.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

112 – Al-Ikhlaas

112 – Al-Ikhlaas (1) በል «እርሱ አላህ አንድ ነው፡፡ (1) Say: He is Allah, the One; (2) «አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው፡፡ (2)…

96 – Al-Alaq

96 – Al-Alaq (1) አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም፡፡ (1) Read in the name of your Lord Who created, (2) ሰውን…

ሱረቱ አል ዩኑስ አማርኛ ቁርአን Free Amharic Quran 10 Yunus

ሱረቱ አል ዩኑስ አማርኛ ቁርአን Free Amharic Quran 10 Yunus الر ۚ تِلْكَ آيَاتُ الْكِتَابِ الْحَكِيمِ  [1] (1) አ.ለ.ረ (አሊፍ…