Default Image
11, Dec 2023
56 – Al-Waaqia

56 – Al-Waaqia

(1) መከራይቱ በወደቀች ጊዜ፡፡(1) When the Inevitable Event comes to pass,
(2) ለመውደቋ አስተባባይ (ነፍስ) የለችም፡፡(2) there will be none to deny its occurrence;
(3) ዝቅ አድራጊና ከፍ አድራጊ ናት፡፡(3) it will bring some low and raise others up.
(4) ምድር መናወጥን በተናወጠች ጊዜ፡፡(4) When the earth will be shaken violently,
(5) ተራራዎችም መፍፈርፈርን በተፈረፈሩ ጊዜ (እንደተፈጨ ዱቄት በኾኑ ጊዜ)፡፡(5) and the mountains crushed to pieces,
(6) የተበተነ ብናኝ በኾኑም ጊዜ(6) and turn to scattered dust,
(7) ሦስት ዓይነቶችም በኾናችሁ ጊዜ (ታዋርዳለች፤ ታነሳለችም)፡፡(7) then you are sorted into three groups:
(8) የቀኝ ጓዶችም ምን (የተከበሩ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡(8) the people of the right – how blessed will be the people of the right!
(9) የግራ ጓዶችም ምን (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች ናቸው፡፡(9) The people of the left – how miserable will be the people of the left!
(10) (ለበጎ ሥራ) ቀዳሚዎቹም (ለገነት) ቀዳሚዎች ናቸው፡፡(10) And the forerunners [in faith] are the forerunners [in Paradise].
(11) እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡(11) They are the nearest ones [to Allah],
(12) በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ሲኾኑ፡፡(12) in Gardens of Bliss,
(13) ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡(13) many from the early generations,
(14) ከኋለኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡(14) and a few from the later generations.
(15) በተታቱ አልጋዎች ላይ ይኾናሉ፡፡(15) [They will be seated] on jeweled couches,
(16) በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲኾኑ፡፡(16) reclining on them, facing one another.
(17) በእነርሱ ላይ ሁል ጊዜ የማያረጁ ወጣቶች ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡(17) They will be served by immortal youths
(18) ከጠጅ ምንጭም በብርጭቆዎችና በኩስኩስቶች በጽዋም (በእነርሱ ላይ ይዝዞራሉ)፡፡(18) with cups, pitchers, and glasses [of wine] from a flowing spring,
(19) ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡(19) which will neither cause any headache nor intoxication,
(20) ከሚመርጡትም ዓይነት በእሸቶች፡፡(20) along with fruits of their choice,
(21) ከሚሹትም በኾነ የበራሪ ሥጋ (ይዞሩባቸዋል)፡፡(21) and flesh of birds that they may desire.
(22) ዓይናማዎች የኾኑ ነጫጭ ቆንጆዎችም አሏቸው፡፡(22) And [they will have] maidens with wide gorgeous eyes,
(23) ልክ እንደተሸፈነ ሉል መሰሎች የኾኑ፡፡(23) like pristine pearls,
(24) በዚያ ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ዋጋ ይኾን ዘንድ (ይህንን አደረግንላቸው)፡፡(24) as a reward for what they used to do.
(25) በውስጥዋ ውድቅ ንግግርንና መውወንጀልን አይሰሙም፡፡(25) They will not hear therein any idle talk or sinful speech,
(26) ግን ሰላም መባባልን (ይሰማሉ)፡፡(26) except the words of peace, peace.
(27) የቀኝም ጓዶች ምንኛ (የከበሩ) የቀኝ ጓዶች!(27) The people of the right – how blessed will be the people of the right!
(28) በተቀፈቀፈ (እሾህ በሌለው) ቁርቁራ ውስጥ ናቸው፡፡(28) [They will be] amid thornless lote trees,
(29) (ፍሬው) በተነባበረ በሙዝ ዛፍም፡፡(29) and clusters of bananas,
(30) በተዘረጋ ጥላ ሥርም፡፡(30) and shade long-extended,
(31) በሚንቧቧ ውሃ አጠገብም፡፡(31) and flowing water,
(32) ብዙ (ዓይነት) በኾኑ ፍራፍሬዎችም፡፡(32) and abundant fruit –
(33) የማትቋረጥም የማትከለከልም የኾነች፡፡(33) neither ceasing nor restricted –
(34) ከፍ በተደረጉ ምንጣፎችም (ሴቶችም መካከል)፡፡(34) and mattresses raised high [on beds].
(35) እኛ አዲስ ፍጥረት አድርገን (ለእነርሱ) ፈጠርናቸው፡፡(35) Indeed, We have perfectly created them [their spouses],
(36) ደናግሎችም አደረግናቸው፡፡(36) and have made them virgins,
(37) ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎች እኩያዎች (አደረግናቸው)፡፡(37) loving and of equal age,
(38) ለቀኝ ጓዶች (አዘጋጀናቸው)፡፡(38) for the people of the right,
(39) ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡(39) many from the earlier generations,
(40) ከኋለኞቹም ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡(40) and many from the later generations.
(41) የግራ ጓደኞችም ምንኛ (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች! ናቸው፡፡(41) And the people of the left – how wretched will be the people of the left!
(42) በመርዛም ነፋስ በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው፡፡(42) [They will be] in scorching wind and scalding water,
(43) ከጥቁር ጭስም በኾነ ጥላ ውስጥ፡፡(43) in the shade of black smoke,
(44) ቀዝቃዛም መልካምም ያልኾነ፡፡(44) neither cool nor refreshing.
(45) እነርሱ ከዚህ በፊት ቅምጥሎች ነበሩና፡፡(45) Indeed, they used to be in luxuries before,
(46) በታላቅ ኀጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና፡፡(46) and persisted in the gravest sin [of polytheism].
(47) ይሉም ነበሩ፡- «በሞትንና ዐፈር፣ ዐጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ በእርግጥ የምንቀሰቀስ ነን?(47) They used to say, “When we die and become dust and bones, will we really be raised again?
(48) «የፊተኞቹ አባቶቻችንም?»(48) And our forefathers as well?”
(49) በላቸው፡- «ፊተኞቹም ኋለኞቹም፡፡(49) Say, [O Prophet], “Indeed, the former and later generations
(50) «በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው፡፡(50) will be gathered on a predetermined Day.
(51) «ከዚያም እናንተ ጠማሞች አስተባባዮች ሆይ!(51) Then you, O misguided deniers,
(52) « ከዘቁም ዛፍ በእርግጥ በይዎች ናችሁ፡፡(52) will surely eat from the tree of zaqqūm,
(53) «ከእርሷም ሆዶቻችሁን ሞይዎች ናችሁ፡፡(53) filling your bellies with it,
(54) «በእርሱ ላይም ከፈላ ውሃ ጠጪዎች ናችሁ፡፡(54) and drinking scalding water on top of it,
(55) «የተጠሙንም ግመሎች አጠጣጥ ብጤ ጠጪዎች ናችሁ፡፡»(55) drinking like thirsty camels do.”
(56) ይህ በፍርዱ ቀን መስተንግዷቸው ነው፡፡(56) This will be their welcome on the Day of Judgment.
(57) እኛ ፈጠርናችሁ አታምኑምን?(57) It is We Who created you; will you not then believe [in resurrection]?
(58) (በማኅፀኖች) የምታፈሱትን አያችሁን?(58) Have you thought about the semen that you emit?
(59) እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹን ነን?(59) Is it you who create it, or is it We Who are the Creators?
(60) እኛ ሞትን (ጊዜውን) በመካከላችሁ ወሰንን፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡(60) We have ordained death among you, and nothing can overcome us
(61) ብጤዎቻችሁን በመለወጥና በዚያ በማታውቁትም (ቅርጽ) እናንተን በመፍጠር ላይ (አንሸነፍም)፡፡(61) from transforming you and recreating you in forms that you do not know.
(62) የፊተኛይቱንም አፈጣጠር በእርግጥ ዐውቃችኋል፡፡ አትገነዘቡምን?(62) You are well aware of the first creation; why do you not then take heed?
(63) የምትዘሩትንም አያችሁን?(63) Have you thought about what you sow?
(64) እናንተ ታበቅሉታላችሁን? ወይስ እኛ አብቃዮቹ ነን?(64) Is it you who cause it grow, or is it We Who make it grow?
(65) ብነሻ ኖሮ ደረቅ ስብርብር ባደረግነውና የምትደነቁም በኾናችሁ ነበር፡፡(65) If We willed, We could reduce your harvest to crumble, leaving you to wonder and lament,
(66) «እኛ በዕዳ ተያዦች ነን፡፡(66) “We suffered loss,
(67) «በእርግጥም እኛ (ከመጠቀም) የተከለከልን ነን» (ትሉ ነበር)፡፡(67) rather, we are deprived.”
(68) ያንንም የምትጠጡትን ውሃ አየችሁን?(68) Have you thought about the water that you drink?
(69) እናንተ ከደመናው አወረዳችሁትን? ወይስ እኛ አውራጆቹ ነን?(69) Is it you who bring it down from the clouds, or is it We Who bring it down?
(70) ብንሻ ኖሮ መርጋጋ ባደረግነው ነበር፡፡ አታመሰግኑምን?(70) If We willed, We could make it salty; will you not then give thanks?
(71) ያቺንም የምትሰብቋትን እሳት አያችሁን?(71) Have you thought about the fire that you kindle?
(72) እናንተ ዛፏን ፈጠራችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎችዋ ነን?(72) Is it you who produced its trees, or is it We Who produced it?
(73) እኛ (ለገሀናም) ማስታወሻ ለመንገደኞችም መጠቀሚያ አደረግናት፡፡(73) We made it a reminder [of the Hellfire] and a benefit for the travelers.
(74) የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡(74) So glorify the Name of your Lord, the Most Great.
(75) በከዋክብትም መጥለቂያዎች እምላለሁ፡፡(75) I do swear by the positions of the stars –
(76) እርሱም ብታወቁ ታላቅ መሓላ ነው፡፡(76) and this is indeed a great oath, if only you knew –
(77) እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡(77) that this is indeed a noble Qur’an,
(78) በተጠበቀ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡(78) in a well-preserved Record,
(79) የተጥራሩት እንጅ ሌላ አይነካውም፡፡(79) that none can touch except the purified [angels] –
(80) ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡(80) a revelation from the Lord of the worlds.
(81) በዚህ ንግግር እናንተ ቸልተኞች ናችሁን?(81) Do you take this discourse lightly,
(82) ሲሳያችሁንም (ዝናምን) እናንተ የምታስተባብሉት ታደርጋላችሁን?(82) and instead [of thanking Allah] for the provision you are given, you show ingratitude?
(83) (ነፍስ) ጉረሮንም በደረሰች ጊዜ፡፡(83) Then why [are you helpless] when the soul reaches the throat,
(84) እናንተ ያን ጊዜ የምታዩ ስትኾኑ፡፡(84) while you are looking on,
(85) እኛም ግን አታዩም እንጅ ከእናንተ ይልቅ ወደእርሱ የቀረብን ስንኾን፡፡(85) when We are closer to him than you, but you do not see?
(86) የማትዳኙም ከኾናችሁ፡፡(86) If you are not subject to retribution, then why do you not
(87) እውነተኞች እንደ ኾናችሁ (ነፍሲቱን ወደ አካሉ) ለምን አትመልሷትም፡፡(87) bring that [soul] back, if you are truthful?
(88) (ሟቹ) ከባለሟሎቹ ቢኾንማ፡፡(88) If that dying person is one of those who will be brought near to Allah,
(89) (ለእርሱ) ዕረፍት፣ መልካም ሲሳይም፣ የመጠቀሚያ ገነትም አልለው፡፡(89) then [he will have] comfort, fragrance, and a Garden of Bliss.
(90) ከቀኝ ጓዶችም ቢኾንማ፡፡(90) If he is one of the people of the right,
(91) ከቀኝ ጓዶች ስለ ኾንክ ላንተ ሰላም አልለህ (ይባላል)፡፡(91) [He will be told], “Peace be to you, for being one of the people of the right.”
(92) ከሚያስዋሹት ጠማማዎችም ቢኾንማ፡፡(92) But if he is one of the misguided deniers,
(93) ከፈላ ውሃ የኾነ መስተንግዶ አልለው፡፡(93) then he will be welcomed with scalding water,
(94) በገሀነም መቃጠልም (አልለው)፡፡(94) and he will burn in Blazing Fire.
(95) ይህ እርሱ እርግጠኛ እውነት ነው፡፡(95) This is indeed the absolute truth.
(96) የታላቁንም ጌታህን ስም አወድስ፡፡(96) So glorify the name of your Lord, the Most Great.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

32 – As-Sajda

32 – As-Sajda (1) አ.ለ.መ (አሊፍ ላም ሚም)፡፡ (1) Alif Lām Mīm. (2) የመጽሐፉ መወረድ ጥርጥር የለበትም፡፡ ከዓለማት ጌታ ነው፡፡ (2)…

49 – Al-Hujuraat

49 – Al-Hujuraat (1) እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በአላህና በመልክተኛው ፊት (ነፍሶቻችሁን) አታስቀድሙ፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ ሰሚ ዐዋቂ ነውና፡፡ (1) O you who…

ሱረቱ አል ሒጅር አማርኛ ቁርአን // Free Amharic Quran Suretu Al-Hijr

ሱረቱ አል ሒጅር አማርኛ ቁርአን // Free Amharic Quran Suretu Al-Hijr الر ۚ تِلْكَ آيَاتُ الْكِتَابِ وَقُرْآنٍ مُّبِينٍ  [1] (1)…