Default Image
10, Dec 2023
28 – Al-Qasas

28 – Al-Qasas

(1) ጠ.ሰ.መ (ጣ ሲን ሚም)፡፡(1) Tā Sīn Mīm.
(2) ይህቺ ገላጭ ከሆነው መጽሐፍ አንቀጾች ናት፡፡(2) These are the verses of the clear Book.
(3) ከሙሳና ከፈርዖን ዜና እውነተኞች ስንኾን ለሚያምኑ ሕዝቦች ባንተ ላይ እናነባለን፡፡(3) We recount to you part of the story of Moses and Pharaoh in truth for people who believe.
(4) ፈርዖን በምድር ላይ ተንበጣረረ፡፡ ነዋሪዎቿንም የተከፋፈሉ ጓዶች አደረጋቸው፡፡ ከእነርሱ ጭፍሮችን ያዳክማል፡፡ ወንዶች ልጆቻቸውን በብዛት ያርዳል፡፡ ሴቶቻቸውንም ይተዋል፤ እርሱ ከሚያበላሹት ሰዎች ነበርና፡፡(4) Indeed, Pharaoh arrogantly elevated himself in the land and divided its people into different factions; oppressing one group of them, slaughtering their sons and sparing their women alive. He was truly one of those who spread corruption.
(5) በእነዚያም በምድር ውስጥ በተጨቆኑ ላይ ልንለግስ፣ መሪዎችም ልናደርጋቸው ወራሾችም ልናደርጋቸው እንሻለን፡፡(5) But We wanted to bestow favor upon those who were oppressed in the land, and make them leaders and inheritors [of the land],
(6) ለእነርሱም በምድር ላይ ልናስመች ፈርዖንንና ሃማንንም ሰራዊቶቻቸውንም ከእነሱ ይፈሩት የነበሩትን ነገር ልናሳያቸው (እንሻለን)፡፡(6) and to establish them in the land, and to show Pharaoh, Hāmān and their soldiers that which they feared.
(7) ወደ ሙሳም እናት «አጥቢው፣ በርሱም ላይ በፈራሽ ጊዜ በባሕሩ ውስጥ ጣይው አትፈሪም፣ አትዘኝም፣ እኛ ወዳንቺ መላሾቹና ከመልክተኞቹም አድራጊዎቹ ነንና» ማለትን አመለከትን፡፡(7) We inspired the mother of Moses, “Suckle him; but when you fear for him, cast him into the river, and do not fear or grieve. We will surely return him to you, and will make him one of the messengers.”
(8) የፈርዖን ቤተሰቦችም (መጨረሻው) ለእነርሱ ጠላት ሐዘንም ይሆን ዘንድ አነሱት፡፡ ፈርዖንና ሃማንም ሰራዊቶቻቸውም ሀጢአተኞች ነበሩ፡፡(8) Then the household of Pharaoh picked him up, so that he may become an enemy to them and a source of grief. Indeed, Pharaoh, Hāmān and their soldiers were wrongdoers.
(9) የፈርዖንም ሚስት «ለእኔ የዓይኔ መርጊያ ነው፡፡ ለአንተም፡፡ አትግደሉት፡፡ ሊጠቅመን ወይም ልጅ አድርገን ልንይዘው ይከጀላልና» አለች፡፡ እነርሱም (ፍጻሜውን) የማያውቁ ሆነው (አነሱት)፡፡(9) Pharaoh’s wife said, “He is a source of joy for me and you. Do not kill him; he will probably benefit us, or we may adopt him as a son.” They were unaware [of the consequences].
(10) የሙሳም እናት ልብ ባዶ ሆነ፡፡ ከምእምናን ትሆን ዘንድ በልቧ ላይ ባላጠነከርን ኖሮ ልትገልጸው ቀርባ ነበር፡፡(10) The heart of Moses’ mother became restless; she was about to disclose it, had We not reassured her heart so that she would maintain her faith [in Allah’s promise].
(11) ለእኅቱም ተከታተይው አለቻት፡፡ እርሱንም እነሱ የማያውቁ ሲሆኑ በሩቅ ሆና አየችው፡፡(11) She said to his sister, “Keep track of him.” So she watched him from a distance, without them noticing.
(12) (ወደናቱ ከመመለሱ) በፊትም አጥቢዎችን (መጥባትን) በእርሱ ላይ እርም አደረግን፡፡ (እኅቱ) «ለእናንተ የሚያሳድጉላችሁን እነርሱም ለእርሱ ቅን አገልጋዮች የሆኑን ቤተሰቦች ላመልክታችሁን» አለችም፡፡(12) We had already forbidden for him all wet-nurses, then she said, “Shall I direct you to a household who will nurse him for you and take good care of him?”
(13) ወደእናቱም ዓይንዋ እንድትረጋ፣ እንዳታዝንም፣ የአላህም የተስፋ ቃል እርግጥ መሆኑን እንድታውቅ መለስነው፡፡ ግን አብዛኞቻቸው አያውቁም፡፡(13) Then We returned him to his mother, so that she would be comforted and not grieve, and so that she would know that Allah’s promise is true. Yet most of them do not know.
(14) ብርታቱንም በደረሰና በተስተካከለ ጊዜ ጥበብንና ዕውቀትን ሰጠነው፡፡ እንዲሁም መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡(14) When he reached his full strength and maturity, We gave him wisdom and knowledge. This is how We reward those who do good.
(15) ከተማይቱንም ሰዎቿ በዝንጋቴ ጊዜ ላይ ሆነው ሳሉ ገባ፡፡ በእርሷም ውስጥ የሚጋደሉን ሁለት ሰዎችን አገኘ፡፡ ይህ ከወገኑ ነው፤ ይህም ከጠላቱ ነው፡፡ ያም ከወገኑ የሆነው ሰው በዚያ ከጠላቱ በሆነው ሰው ላይ እርዳታን ጠየቀው፡፡ ሙሳም በጡጫ መታው፡፡ ገደለውም፡፡ ይህ ከሰይጣን ሥራ ነው፡፡ እርሱ ግልጽ አሳሳች ጠላት ነውና አለ፡፡(15) Once he entered the city unnoticed by its people, and found two men fighting: one of his own people and the other of his enemies. The one from his own people called him for help against his enemy, so Moses struck him with his fist, causing his death. Moses said, “This is of Satan’s work; he is a sworn enemy who mislead people.”
(16) «ጌታዬ ሆይ! እኔ ነፍሴን በደልኩ፡፡ ለእኔም ማር አለ፡፡» ለእርሱም ምሕረት አደረገለት እርሱ መሓሪ አዛኝ ነውና፡፡(16) He said, “My Lord, I have wronged myself, so forgive me,” Then He forgave him, for He is indeed the All-Forgiving, the Most Merciful.
(17) «ጌታዬ ሆይ! በእኔ ላይ በመለገስህ ይሁንብኝ (ከስህተቴ እጸጸታለሁ)፤ ለአመጸኞችም ፈጽሞ ረዳት አልሆንም አለ፡፡(17) He said, “My Lord, because of the blessings that You have bestowed upon me, I will never be a supporter to the wicked.”
(18) በከተማይቱም ውስጥ ፈሪ የሚጠባበቅ ሆኖ አደረ፡፡ በድንገትም ያ ትላንት እርዳታን የጠየቀው ሰው በጩኸት እርዳታን ይጠይቀዋል፡፡ ሙሳ ለርሱ «አንተ በእርግጥ ግልጽ ጠማማ ነህ» አለው፡፡(18) Then he became fearful and vigilant in the city; suddenly the one who sought his help the day before cried out to him again for help. Moses said to him, “You are clearly a troublemaker.”
(19) (ሙሳ) ያንን እርሱ ለሁለቱም ጠላት የሆነውን ሰው በኃይል ሊይዘው በፈለገም ጊዜ «ሙሳ(19) When he was about to strike the one who was an enemy to both of them, he said, “O Moses, do you want to kill me as you killed that person yesterday? You only want to be a tyrant in the land, and you do not want to be one of those who put things right!”
(20) ከከተማይቱም ዳርቻ አንድ ሰው እየሮጠ መጣ፡፡ «ሙሳ ሆይ! ሹማምንቶቹ ሊገድሉህ ባንተ ይመካከራሉና ውጣ፡፡ እኔ ላንተ ከመካሪዎች ነኝና» አለው፡፡(20) Then there came a man rushing from the farthest end of the city, and said, “O Moses, the chiefs are conspiring to kill you, so leave. I am giving you sincere advice.”
(21) የፈራና የሚጠባበቅ ሆኖም ከእርሷ ወጣ፡፡ «ጌታዬ ሆይ! ከበደለኞቹ ሕዝቦች አድነኝ» አለ፡፡(21) So he left the city, fearful and vigilant. He said, “My Lord, save me from the wrongdoing people.”
(22) ወደ መድየን አቅጣጫ ፊቱን ባዞረ ጊዜም «ጌታዬ ቀጥተኛውን መንገድ ሊመራኝ እከጅላለሁ» አለ፡፡(22) When he headed towards Midian, he said, “My Lord will surely guide me to a straight way.”
(23) ወደ መድየንም ውሃ በመጣ ጊዜ በእርሱ ላይ ከሰዎች ጭፍሮችን (መንጋዎቻቸውን) የሚያጠጡ ሆነው አገኘ፡፡ ከእነርሱ በታችም (ከውሃው መንጎቻቸውን) የሚከለክሉን ሁለት ሴቶች አገኘ፡፡ «ነገራችሁ ምንድን ነው» አላቸው፡፡ «እረኞቹ ሁሉ (መንጋዎቻቸውን) እስከሚመልሱ አናጠጣም፡፡ አባታችንም ትልቅ ሽማግሌ ነው» አሉት፡፡(23) When he arrived at the well of Midian, he found a crowd of people watering [their flocks] and found apart from them two women holding [their flocks] back. He said, “What is the matter with you?” They said, “We cannot water [them] until the shepherds take [their flocks] away, and our father is a very old man.”
(24) ለሁለቱም አጠጣላቸው፡፡ ከዚያም ወደ ጥላው ዘወር አለ፡፡ «ጌታዬ ሆይ! እኔ ከመልካም ነገር ወደኔ ለምታወርደው ፈላጊ ነኝ» አለ፡፡(24) So he watered [their flocks] for them, then he turned to the shade and said, “My Lord, I am desperately in need of whatever good You may send down to me.”
(25) ከሁለቱ አንደኛይቱም ከሐፍረት ጋር የምትኼድ ሆና መጣችው፡፡ «አባቴ ለእኛ ያጠጣህልንን ዋጋ ሊሰጥህ ይጠራሃል» አለችው፡፡ ወደእርሱ በመጣና ወሬውን በእርሱ ላይ በተረከለትም ጊዜ «አትፍራ ከበደለኞቹ ሕዝቦች ድነሃል» አለው፡፡(25) Then one of the two women came to him, walking modestly. She said, “My father is inviting you so that he may reward you for watering [our flocks] for us.” When he came to him and told him the whole story, he said, “Have no fear. You are now safe from the wrongdoing people.”
(26) ከሁለቱ አንደኛይቱም «አባቴ ሆይ ቅጠረው፡፡ ከቀጠርከው ሰው ሁሉ በላጩ ብርቱው ታማኙ ነውና» አለችው፡፡(26) One of the two daughters said, “O dear father, hire him; the best one you can hire is the strong and trustworthy.”
(27) «ስምንትን ዓመታት ልታገለግለኝ እኔ ከእነዚህ ሁለት ሴቶቸ ልጆቼ አንዲቱን ላጋባህ እሻለሁ፡፡ ዐስርን ብትሞላም ከአንተ ነው፡፡ ባንተ ላይ ማስቸገርንም አልሻም፡፡ አላህ የሻ እንደ ኾነ ከመልካሞቹ ሰዎች ኾኜ ታገኘኛለህ» አለው፡፡(27) He said, “I would like to give you one of these two daughters of mine in marriage, provided that you serve me for eight years; if you complete ten, it will be of your own free will. I do not want to make things difficult for you. You will find me, if Allah wills, from among the righteous.”
(28) (ሙሳም) «ይህ (ውለታ) በእኔና ባንተ መካከል (ረጊ) ነው፡፡ ከሁለቱ ጊዜያቶች ማንኛውንም ብፈጽም በእኔ ላይ ወሰን ማለፍ የለም፡፡ አላህም በምንለነው ላይ ምስክር» ነው አለ፡፡(28) Moses said, “Let that be the agreement between me and you. Whichever of the two terms I complete, there will be no further obligation on me, and Allah is Witness over what we say.”
(29) ሙሳም ጊዜውን በጨረሰና ከቤተሰቦቹ ጋር በኼደ ጊዜ ከጡር ተራራ ጎን እሳትን አየ፡፡ ለቤተሰቡ (እዚህ) «ቆዩ፡፡ እኔ እሳትን አየሁ፡፡ ከእርሷ ወሬን ወይም ትሞቁ ዘንድ ከእሳት ትንታግን አመጣላችኋለሁ» አለ፡፡(29) When Moses had completed the term and was traveling with his family, he spotted a fire in the direction of Mount Tūr. He said to his family, “Stay here; I have spotted a fire. Perhaps I will bring you from there some news or a brand of fire so that you may warm yourselves.”
(30) በመጣትም ጊዜ ከሸለቆው ቀኝ ዳርቻ ከዛፊቱ በኩል በተባረከችው ስፍራ ውስጥ «ሙሳ ሆይ! እኔ የዓለማት ጌታ አላህ እኔ ነኝ» በማለት ተጠራ፡፡(30) But when he came to it, he was called from the tree in the sacred ground on the right side of the valley: “O Moses, I am Allah, the Lord of the worlds.
(31) «በትርህንም ጣል» (ተባለ)፡፡ እንደ ትንሽ እባብ ስትስለከለክ ባያትም ጊዜ ወደ ኋላ ዞሮ ሸሸ፤ አልተመለሰምም፡፡ «ሙሳ ሆይ! ተመለስ አትፍራም፤ አንተ ከጥብቆቹ ነህና» (ተባለም)፡፡(31) Throw down your staff.” But when he saw it slithering as if it were a snake, he turned and ran away without looking back. [Allah said], “O Moses, come back, and have no fear; you are perfectly safe.
(32) «እጅህን በአንገትጌህ ውስጥ አግባ፡፡ ያለ ነውር ነጭ ሆና ትወጣለችና፡፡ ክንፍህንም ከፍርሃት (ለመዳን) ወዳንተ አጣብቅ፡፡ እነዚህም ከጌታህ የሆኑ ወደ ፈርዖንና ወደ መኳንንቶቹ የሚደርሱ ሁለት አስረጅዎች ናቸው፡፡ እነርሱ አመጸኞች ሕዝቦች ነበሩና፡፡»(32) Put your hand into your garment, it will come out shining white without blemish; and draw your arms tight to you to calm your fear. These are two proofs from your Lord to Pharaoh and his chiefs, for they are indeed a rebellious people.”
(33) (ሙሳ) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔ ከእነርሱ ነፍስን ገድያለሁ፡፡ ስለዚህ እንዳይገድሉኝ እፈራለሁ፡፡(33) Moses said, “My Lord, I have killed one of their men, and I fear that they may kill me.
(34) «ወንድሜም ሃሩን እርሱ ምላሱ ከእኔ የተባ ነው፡፡ እውነተኛነቴንም የሚያረጋግጥልኝ ረዳት ኾኖ ከእኔ ጋር ላከው፡፡ እኔ ሊያስተባብሉኝ እፈራለሁና፡፡»(34) My brother Aaron is more eloquent than me in speech, so send him with me as a helper to confirm my words, for I fear that they may reject me.”
(35) (አላህም) «ጡንቻህን በወንድምህ በእርግጥ እናበረታለን፡፡ ለሁለታችሁም ስልጣንን እናደርጋለን፡፡ ወደእናንተም (በመጥፎ) አይደርሱም፡፡ በተዓምራቶቻችን (ኺዱ)፡፡ እናንተና የተከተላችሁም ሁሉ አሸናፊዎች ናችሁ» አላቸው፡፡(35) Allah said, “We will strengthen you through your brother and give you both power, so they cannot harm you. With Our signs, you and your followers will prevail.”
(36) ሙሳም በታምራቶቻችን ግልጽ ኾነው በመጣባቸው ጊዜ «ይህ የተቀጠፈ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ ይህንንም በመጀመሪያዎቹ አባቶቻችን ውስጥ አልሰማንም» አሉ፡፡(36) When Moses came to them with Our clear signs, they said, “This is nothing but fabricated magic; we have not heard of this from our earlier ancestors.”
(37) ሙሳም «ጌታዬ ከእርሱ ዘንድ በቀጥታው መንገድ የመጣውን ሰው ምስጉኒቱም አገር ለእርሱ የምትኾንለትን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡ እነሆ በደለኞቹ አይድኑም» አለ፡፡(37) Moses said, “My Lord knows best who has come with guidance from Him and who will have the best abode in the end. The wrongdoers will never succeed.”
(38) ፈርዖንም «እናንተ ጭፍሮች ሆይ! ከእኔ ሌላ ለእናንተ አምላክን ምንም አላወቅሁም፡፡ ሃማንም ሆይ! ጭቃን ለእኔ አቃጥልልኝ፤ (ጡብ ሥራልኝ)፡፡ ለእኔም ከፍተኛ ሕንጻን ሥራልኝ፡፡ ወደ ሙሳ አምላክ ልወጣ እከጅላለሁና፡፡ እኔም ከውሸታሞቹ መኾኑን እጠረጥረዋለሁ» አለ፡፡(38) Pharaoh said, “O chiefs, I do not know for you any god other than myself. So bake for me bricks out of clay, O Hāmān, and build for me a tower so that I may have a look at the God of Moses, for I think he is a liar.”
(39) እርሱም ሰራዊቶቹም በምድር ላይ ያለ አግባብ ኮሩ፡፡ እነርሱም ወደእኛ የማይመለሱ መኾናቸውን ጠረጠሩ፡፡(39) He and his soldiers were arrogant in the land without any right, and thought that they would not be brought back to Us.
(40) እርሱንም ሰራዊቱንም በጥብቅ ያዝናቸው፡፡ በባሕርም ውስጥ ጣልናቸው፡፡ የበደለኞች መጨረሻም፤ እንዴት እንደ ነበረ ተመልከት፡፡(40) So We seized him and his soldiers and flung them into the sea. See how was the end of the wrongdoers!
(41) ወደ እሳት የሚጠሩ መሪዎችም አደረግናቸው፡፡ በትንሣኤም ቀን አይርረዱም፡፡(41) We made them leaders calling to the Fire, and on the Day of Resurrection they will not be helped.
(42) በይህችም በቅርቢቱም ዓለም ውስጥ እርግማንን አስከተልናቸው፡፡ በትንሣኤም ቀን እነሱ ከሚባረሩት ናቸው፡፡(42) We caused a curse to pursue them in this world, and on the Day of Resurrection they will be among those who are despised.
(43) የፊተኞቹን የክፍለ ዘመናት ሕዝቦችም ከአጠፋን በኋላ ለሰዎች የልብ ብርሃን መሪም እዝነትም ሲኾን ይገሰጹ ዘንድ ለሙሳ መጽሐፉን በእርግጥ ሰጠነው፡፡(43) We gave Moses the Scripture after destroying earlier nations, as an insight for mankind, and a guidance and mercy, so that they may take heed.
(44) ወደ ሙሳም ትዕዛዝን ባወረድንለት ጊዜ (ከተራራው) በምዕራባዊው ጎን አልነበርክም ከተጣዱትም አልነበርክም፡፡(44) You were not [O Prophet] on the western side [of the mountain] when We gave Moses Our commandment, nor did you witness that event.
(45) ግን እኛ (ከእርሱ በኋላ) የክፍለ ዘመናትን ሰዎች አስገኘን፡፡ በእነሱም ላይ ዕድሜዎች ተራዘሙ፡፡ በመድየንም ሰዎች ውስጥ ተቀማጭ በእነሱ ላይ አንቀጾቻችን የምታነብ አልነበርክም፡፡ ግን እኛ ላኪዎችህ ኾንን፡፡(45) But We brought forth many generations [after Moses], and a long time passed on them. And you [O Prophet] did not dwell among the people of Midian, rehearsing with them Our verses, but it is We Who sent you as a messenger [and revealed to you their stories].
(46) በጠራነውም ጊዜ በጡር ጎን አልነበርክም፡፡ ግን ከአንተ በፊት ምንም አስፈራሪ ያልመጣቸውን ሕዝቦች ታስፈራራ ዘንድ ከጌታህ በኾነ ችሮታ (ላክንህ) ሊገሰጹ ይከጀላልና፡፡(46) You were not at the side of Mount Tūr when We called out [to Moses]. But [you have been sent] as a mercy from your Lord, to warn a people to whom no warner had come before you, so that they may take heed.
(47) እጆቻቸውም ባሳለፉት ምክንያት መከራ የምትነካቸውና «ጌታችን ሆይ! አንቀጾችህን እንድንከተል ከምእምናንም እንድንኾን ወደኛ መልክተኛን አትልክም ኖሯልን» የሚሉ ባልኾኑ ኖሮ (አንልክም ነበር)፡፡(47) So they would not say – if struck by a calamity because of what their hands have sent forth, “Our Lord, if only You had sent us a messenger, so we could follow Your verses and be among the believers?”
(48) እውነቱም ከእኛ ዘንድ በመጣላቸው ጊዜ «ለሙሳ የተሰጠው ብጤ አይስሰጠውም ኖሯልን» አሉ፡፡ «ከዚህ በፊት ሙሳ በተሰጠው አልካዱምን የተረዳዱ ሁለት ድግምቶች ናቸው» አሉ፡፡(48) But when the truth came to them from Us, they said, “If only he was given the like of what was given to Moses before.” Did they not reject what was given to Moses before? They say, “Both [revelations] are works of magic, supporting each other”, adding, “We truly reject both of them.”
(49) «ከአላህ ዘንድ የኾነን መጽሐፍ እርሱ ከሁለቱም ይበልጥ ቅን የኾነን አምጡ፡፡ እውነተኞች እንደ ኾናችሁ (ብታመጡት) እከተለዋለሁ» በላቸው፡፡(49) Say, “Then bring a scripture from Allah which is better in guidance than these two so that I may follow it, if you are truthful.”
(50) እሺ ባይሉህም፤ የሚከተሉት፤ ዝንባሌዎቻቸውን ብቻ መኾኑን ዕወቅ፡፡ ከአላህም የኾነ መመሪያ ሳይኖረው ዝንባሌውን ከተከተለ ሰው ይበልጥ የጠመመ አንድም የለም፡፡ አላህ በደለኞች ሕዝቦችን አይመራምና፡፡(50) But if they do not respond to you, then know that they only follow their desires. Who is more astray than one who follows his desire without any guidance from Allah? Indeed, Allah does not guide the wrongdoing people.
(51) ይገሰጹም ዘንድ ቃልን (ቁርኣንን በያይነቱ) ለእነርሱ በእርግጥ አስከታተልን፡፡(51) Now We have conveyed Our Word to them, so that they may take heed.
(52) እነዚያ ከእርሱ በፊት መጽሐፍን የሰጠናቸው እነርሱ በእርሱ ያምናሉ፡፡(52) As for those whom We gave the Scripture before this [Qur’an], they do believe in it.
(53) በእነሱ ላይ በሚነበብላቸውም ጊዜ «በእርሱ አምነናል፡፡ እርሱ ከጌታችን የኾነ እውነት ነው፡፡ እኛ ከርሱ በፊት ሙስሊሞች ነበርን» ይላሉ፡፡(53) When this [Qur’an] is recited to them, they say, “We believe in it, for it is the truth from our Lord. We had already submitted [as Muslims even] before this.”
(54) እነዚያ በመታገሳቸው ዋጋቸውን ሁለት ጊዜ ይስሰጣሉ፡፡ ክፉውንም ነገር በበጎ ምግባር ይገፈትራሉ፡፡ ከሰጠናቸውም ሲሳይ ይለግሳሉ፡፡(54) They will be given their reward twice for their patience, repelling evil with good, and for spending out of what We have provided for them.
(55) ውድቅንም ቃል በሰሙ ጊዜ ከእርሱ ይርቃሉ፡፡ «ለእኛ ሥራዎቻችን አሉን፡፡ ለናንተም ሥራዎቻችሁ አሏችሁ፡፡ ሰላም በእናንተ ላይ (ይኹን) ባለጌዎችን አንፈልግም» ይላሉ፡፡(55) When they hear vain talk, they turn away from it and say, “We are accountable for our deeds and you for yours. Peace [is our response] to you! We do not want [to be with] the ignorant.”
(56) አንተ የወደድከውን ሰው ፈጽሞ አታቀናም፡፡ ግን አላህ የሚሻውን ሰው ያቀናል እርሱም ቅኖቹን ዐዋቂ ነው፡፡(56) You cannot guide whoever you like, but Allah guides whom He wills, and He knows best who will be guided.
(57) «ከአንተ ጋር ቅንን መንገድ ብንከተል ከምድራችን እንባረራለን» አሉም፡፡ ከእኛ ዘንድ (የተሰጠ) ሲሳይ ሲሆን የነገሩ ሁሉ ፍሬዎች ወደእርሱ የሚነዱበትን ጸጥተኛ ክልል (መካን) ለእነሱ አላስመቸናቸውምን ግን አብዛኞቻቸው አያውቁም፡፡(57) They say, “If we follow the guidance with you [O Prophet], we will be snatched away from our land.” Have We not established for them a safe sanctuary [in Makkah] to which fruits of all kinds are brought as provision from Us? But most of them do not know.
(58) ከከተማም ኑሮዋን (ምቾቷን) የካደችን (ከተማ) ያጠፋናት ብዙ ናት፡፡ እነዚህም ከእነሱ በኋላ ጥቂት ጊዜ እንጅ ያልተኖረባቸው ሲኾኑ መኖሪያዎቻቸው ናቸው፡፡ እኛም (ከእነርሱ) ወራሾች ነበርን፡፡(58) How many a town We have destroyed that were arrogant due to their affluence! Those are their dwellings which were never inhabited after them except briefly. It is We Who were the Inheritors.
(59) ጌታህም ከተሞችን በዋናዋ (ከተማ) ውስጥ አንቀጾቻችንን በእነሱ ላይ የሚያነብ መልክተኛን እስከሚልክ ድረስ አጥፊ አልነበረም፡፡ ከተሞችንም ባለቤቶቿ በዳዮች ሆነው እንጅ አጥፊዎች አልነበርንም፡፡(59) Your Lord would never destroy towns without first sending to their main city a messenger, reciting to them Our verses. Nor would We destroy towns unless their people were wrongdoers.
(60) ከማንኛውም ነገር የተሰጣችሁት፤ የቅርቢቱ ሕይወት ጥቅምና ጌጧ ነው፡፡ አላህ ዘንድ ያለውም (ምንዳ) በጣም በላጭና ዘውታሪ ነው አታውቁምን(60) Whatever you have been given is only an enjoyment and adornment of the life of this world, but what is with Allah is better and more lasting. Will you not then understand?
(61) መልካምን ተስፋ ቃል የገባንለትና እርሱም አግኚው የሆነ ሰው የቅርቢቱን ሕይወት ጥቅም እንዳስመቸነውና ከዚያም እርሱ በትንሣኤ ቀን (ለእሳት) ከሚቀረቡት እንደ ኾነው ሰው ነውን(61) Is one whom We promised a good promise – which he is going to obtain – like one whom We gave the pleasure of the life of this world, then on the Day of Resurrection he will be among those summoned [to Hellfire]?
(62) (አላህ) የሚጠራባቸውንና እነዚያ ተጋሪዎቼ ትሏቸው የነበራችሁት የት ናቸው የሚልበትን ቀን (አስታውስ)፡፡(62) And [beware of] the Day when He will call out to them and say, “Where are those whom you claimed to be My partners?”
(63) እነዚያ በእነርሱ ላይ ቃሉ የተረጋገጠባቸው ይላሉ «ጌታችን ሆይ! እነዚህ እነዚያ ያጠመምናቸው ናቸው፡፡ እንደጠመምን አጠመምናቸው፡፡ (ከእነሱ) ወዳንተ ተጥራራን፡፡ እኛን ይግገዙ አልነበሩም፡፡(63) Those against whom the word will be fulfilled will say, “Our Lord, these are the ones whom we led astray; we led them astray as we ourselves went astray. We disassociate ourselves [from them] before You; it was not us that they used to worship.”
(64) «(ለአላህ) የምታጋሯቸውንም ጥሩ» ይባላሉ፤ ይጠሯቸዋልም፡፡ ግን ለእነርሱ አይመልሱላቸውም፡፡ ቅጣቱንም ያያሉ፡፡ እነርሱ ይመሩ በነበሩ ኖሮ (አያዩትም ነበር)፡፡(64) Then they will be told, “Call upon your [so-called] partners [for help].” They will call upon them, but will receive no response. They will see the punishment, wishing that they had followed guidance.
(65) «የሚጠራባቸውንና ለመልክተኞቹም ምንን መለሳችሁ» የሚልበትን ቀን (አስታውስ)፡፡(65) On the Day when He will call out to them, saying, “What response did you give to the messengers?”
(66) በዚያም ቀን ወሬዎቹ ሁሉ በእነርሱ ላይ ይሰውሩባቸዋል፡፡ እነርሱም አይጠያየቁም፡፡(66) They will be dumbstruck on that Day, not even able to ask one another.
(67) የተጸጸተና ያመነ ሰውማ መልካምንም የሠራ ከሚድኑት ሊኾን ይከጀላል፡፡(67) But whoever repents and believes, and does righteous deeds, he will be among the successful.
(68) ጌታህም የሚሻውን ይፈጥራል፤ ይመርጣልም፡፡ ለእነርሱ (ለሰዎቹ) ምርጫ የላቸውም፡፡ አላህ ከማይግገባው ሁሉ ጠራ፡፡ ከሚያጋሯቸውም ላቀ፡፡(68) Your Lord creates and chooses what He wills; they have no choice. Glorified is Allah and Exalted is He far above what they associate with Him.
(69) ጌታህም ልቦቻቸው የሚደብቁትንና የሚገልጹትን ሁሉ ያውቃል፡፡(69) Your Lord knows all that their hearts conceal and all that they reveal.
(70) እርሱም አላህ ነው፡፡ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ ምስጋና በመጀመሪያይቱም በመጨረሻይቱም ዓለም ለእርሱ ብቻ ነው፡፡ ፍርዱም የእርሱ ብቻ ነው፡፡ ወደእርሱም ትመለሳላችሁ፡፡(70) He is Allah: none has the right to be worshiped except Him. All praise belongs to Him in this life and the Hereafter. His is the Judgment, and to Him you will all be returned.
(71) አያችሁን (ንገሩኝ) «አላህ በእናንተ ላይ ሌሊትን እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ ዘውታሪ ቢያደርገው ከአላህ ሌላ ብርሃንን የሚያመጣላችሁ አምላክ ማነው አትሰሙምን» በላቸው፡፡(71) Say, “What do you think, if Allah were to make the night perpetual for you until the Day of Resurrection, which god other than Allah could bring you shining light? Do you not then listen?”
(72) አያችሁን «አላህ በእናንተ ላይ ቀንን እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ ዘውታሪ ቢያደርገው ከአላህ ሌላ በውስጡ የምታርፉበትን ሌሊት የሚያመጣላችሁ አምላክ ማን ነው (ንገሩኝ) አታስተውሉምን» በላቸው፡፡(72) Say, “What do you think, if Allah were to make the day perpetual for you until the Day of Resurrection, which god other than Allah could bring you night to rest in? Do you not then see?”
(73) ከችሮታውም ለእናንተ ሌሊትንና ቀንን በውስጡ ልታርፉበት፣ ከትሩፋቱም ልትፈልጉበት፣ አመስገኞችም ልትኾኑ አደረገላችሁ፡፡(73) It is out of His mercy that He made for you the night and day, so that you may rest therein and seek of His bounty, and so that you may be grateful.
(74) የሚጠራባቸውንም ቀንና «እነዚያ ተጋሪዎቼ ትሏቸው የነበራችሁት የት ናቸው» የሚልበትን (አስታውስ)፡፡(74) And [beware of] the Day when He will call out to them and say, “Where are those whom you claimed to be My partners?”
(75) ከሕዝቦችም ሁሉ መስካሪን እናወጣለን፡፡ (ያን ጊዜ) እውነተኛውም አምላክነት ለአላህ ብቻ መኾኑን ያውቃሉ፡፡ ይቀጣጥፉት የነበሩትም ከእነርሱ ይጠፋቸዋል፡፡(75) We will bring forth from every nation a witness and say, “Bring your proof.” They will then know that the truth is with Allah, and all [false gods] that they used to invent will be lost from them.
(76) ቃሩን ከሙሳ ነገዶች ነበር፡፡ በእነርሱም ላይ አመጸ፡፡ ከድልቦችም ያንን መከፈቻዎቹ ብቻ የኃይል ባለቤቶች የኾኑ ጭፍሮችን (ሸክሙ) የሚከብድን ሰጠነው፡፡ ወገኖቹ ለእርሱ አትኩራ፤ አላህ ኩራተኞችን አይወድምና ባሉት ጊዜ (አስታውስ)፡፡(76) Indeed, Korah was one of the people of Moses, but he behaved arrogantly towards them. We had given him such treasures that their keys would weigh down a group of strong men. When his people said to him, “Do not exult, for Allah does not like the exultant.
(77) «አላህም በሰጠህ ሀብት የመጨረሻይቱን አገር ፈልግ፡፡ ከቅርቢቱም ዓለም ፋንታህን አትርሳ፡፡ አላህም ወደ አንተ መልካምን እንዳደረገልህ (ለሰዎች) መልካምን አድርግ፡፡ በምድርም ውስጥ ማጥፋትን አትፈልግ፡፡ አላህ አጥፊዎችን አይወድምና» (አሉት)፡፡(77) Rather, seek with what Allah has given you the abode of the Hereafter, without forgetting your share of this world, and do good as Allah has done good to you, and do not seek to spread corruption in the land, for Allah does not like those who spread corruption.”
(78) (ሀብቱን) «የተሰጠሁት እኔ ዘንድ ባለው እውቀት ብቻ ነው አለ፡፡ አላህ ከእርሱ በፊት ከክፍለ ዘመናት ሰዎች በኀይል ከእርሱ ይበልጥ የበረቱትን (ሀብትን) በመሰብሰብም ይበልጥ የበዙትን በእርግጥ ያጠፋ መኾኑን አያውቅምን አመጸኞችም ከኀጢኣቶቻቸው (ምሕረት የሚከተለውን ጥያቄ) አይጠየቁም፡፡(78) He said, “I have been given all this because of the knowledge that I have.” Did he not know that Allah destroyed some generations before him who were superior to him in power and greater in accumulating [wealth]? There will be no need for the wicked to be asked about their sins.
(79) በሕዝቦቹም ላይ በጌጡ ውስጥ ኾኖ ወጣ፡፡ እነዚያ ቅርቢቱን ሕይወት የሚፈልጉት «ወይ ምኞታችን! ቃሩን የተሰጠው ብጤ ምነው ለእኛ በኖረን፤ እርሱ የታላቅ ዕድል ባለቤት ነውና» አሉ፡፡(79) He came out before his people in all his glamor. Those who desired the life of this world said, “Oh, would that we had the like of what Korah has been given! He is indeed a man of great fortune.”
(80) እነዚያም ዕውቀትን የተሰጡት «ወዮላችሁ! የአላህ ምንዳ ለአመነ ሰው መልካምንም ለሠራ በላጭ ነው፡፡ ታጋሾችም እንጅ ሌላው አያገኛትም» አሉ፡፡(80) But those who were given knowledge said, “Woe to you! Allah’s reward is better for those who believe and do righteous deeds. But none will attain this except those who are steadfast.”
(81) በእርሱም በቤቱም ምድርን ደረባን፡፡ ለእርሱም ከአላህ ሌላ የሚረዱት ጭፍሮች ምንም አልነበሩትም፡፡ ከሚርረዱትም አልነበረም፡፡(81) Then We caused the earth to swallow him and his house. There was no one to help him against Allah, nor was he able to help himself.
(82) እነዚያም በትላንትናው ቀን ስፍራውን ይመኙ የነበሩት «ወይ ጉድ! ለካ አላህ ከባሮቹ ለሚሻው ሰው ሲሳይን ያሰፋል፤ ያጠባልም፡፡ አላህ በእኛ ላይ (በእምነት) ባልለገሰልን ኖሮ ምድርን በእኛ ላይ በገለበጠብን ነበር፡፡ ወይ ጉድ! ከሓዲዎች አይድኑም» የሚሉ ኾነው አነጉ፡፡(82) Those who had wished for his position the day before started saying, “Oh, it is surely Allah Who extends provisions to whom He wills or restricts it. If Allah had not favored us, He could have caused the earth to swallow us too. Oh, indeed the disbelievers will never succeed.”
(83) ይህች የመጨረሻይቱ አገር ለእነዚያ በምድር ውስጥ ኩራትንና ማመፅን ለማይፈልጉት እናደርጋታለን፡፡ ምስጉኒቱም መጨረሻ ለጥንቁቆቹ ናት፡፡(83) That is the abode of the Hereafter We will assign to those who neither seek superiority nor corruption on earth. The best outcome is for those who fear Allah.
(84) በደግ ሥራ የመጣ ሰው ለእርሱ ከእርሷ በላጭ ምንዳ አልለው፡፡ በክፉም ሥራ የመጡ ሰዎች እነዚህ መጥፎዎችን የሠሩ ይሠሩት የነበሩትን እንጅ አይመነዱም፡፡(84) Whoever comes with a good deed will be rewarded with what is better, and whoever comes with an evil deed, the evildoers will only be recompensed for what they used to do.
(85) ያ ቁርኣንን የተከፋፈለ ኾኖ ባንተ ላይ ያወረደው (አምላክ) ወደ መመለሻ (ወደመካ) በእርግጥ መላሽህ ነው፡፡ «ጌታዬ በቅን መንገድ የመጣውን ሰውና እርሱም በግልጽ ስሕተት ውስጥ የኾነውን ሰው ዐዋቂ ነው» በላቸው፡፡(85) Indeed, the One Who has ordained for you the Qur’an will bring you back home [to Makkah]. Say, “My Lord knows best who has come with guidance and who is clearly misguided.”
(86) መጽሐፉ ወዳንተ መወረዱን ተስፋ የምታደርግ አልነበርክም፡፡ ግን ከጌታህ ችሮታ (ተወረደልህ)፡፡ ለከሓዲዎችም በፍጹም ረዳት አትኹን፡፡(86) You were not expecting the Book to be revealed to you, but it was a mercy from your Lord. So never be a supporter to the disbelievers.
(87) ከአላህም አንቀጾች ወዳንተ ከተወረዱ ጊዜ በኋላ አያግዱህ፡፡ ወደ ጌታህም (ሰዎችን) ጥራ፡፡ ከአጋሪዎቹም አትኹን፤(87) Do not let them turn you away from Allah’s verses after they have been sent down to you. Rather, call people to your Lord, and never be among those who associate partners with Allah.
(88) ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አትግገዛ፡፡ ከእርሱ በቀር አምላክ የለም፡፡ ነገሩ ሁሉ ከአላህ በቀር ጠፊ ነው፡፡ ፍርዱ የርሱ፤ ብቻ ነው፡፡ ወደእርሱም ትመለሳላችሁ፡፡(88) Do not invoke with Allah another god; none has the right to be worshiped except Him. Everything will perish except Him. His is the Judgment and to Him you will all be brought back.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

95 – At-Tin

95 – At-Tin (1) በበለስና በዘይት ወይራ እምላለሁ፡፡ (1) By the fig and the olive [of Jerusalem], (2) በሲኒን ተራራም፤ (2)…

47 – Muhammad

47 – Muhammad (1) እነዚያ የካዱ ከአላህ መንገድም የከለከሉ (አላህ) ሥራዎቻቸውን አጠፋባቸው፡፡ (1) Those who disbelieve and prevent others from Allah’s way,…

46 – Al-Ahqaf

46 – Al-Ahqaf (1) ሐ.መ (ሓ ሚም)፡፡ (1) Hā Mīm. (2) የመጽሐፉ መወረድ አሸናፊ ጥበበኛ ከኾነው አላህ ነው፡፡ (2) The revelation…