Default Image
10, Dec 2023
44 – Ad-Dukhaan

44 – Ad-Dukhaan

(1) ሐ.መ (ሓ ሚም)፡፡(1) Hā Mīm.
(2) አብራሪ በኾነው መጽሐፍ እንምላለን፡፡(2) By the clear Book.
(3) እኛ (ቁርኣኑን) በተባረከች ሌሊት ውስጥ አወረድነው፡፡ እኛ አስፈራሪዎች ነበርንና፡፡(3) Indeed, We sent it down on a blessed night, We have been warning about.
(4) በውስጧ የተወሰነው ነገር ሁሉ ይልለያል፡፡(4) On that night, every matter of wisdom is determined
(5) ከእኛ ዘንድ የኾነ ትእዛዝ ሲኾን (አወረድነው)፡፡ እኛ (መልክተኞችን) ላኪዎች ነበርን፡፡(5) by Our command. We have always sent messengers.
(6) ከጌታህ በኾነው ችሮታ (ተላኩ)፡፡ እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡(6) as a mercy from your Lord. He is indeed the All-Hearing, the All-Knowing,
(7) የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ከኾነው (ተላኩ)፡፡ የምታረጋግጡ እንደኾናችሁ (ነገሩ እንዳልነው መኾኑን እወቁ)፡፡(7) Lord of the heavens and earth and all that is between them, if only you had sure faith.
(8) ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ ሕያው ያደርጋል፡፡ ይገድላልም፡፡ ጌታችሁ የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው፡፡(8) None has the right to be worshiped except Him, Who gives life and causes death – your Lord, and the Lord of your forefathers.
(9) በእውነቱ እነርሱ የሚጫወቱ ሲኾኑ በመጠራጠር ውስጥ ናቸው፡፡(9) But they are in doubt, amusing themselves.
(10) ሰማይም በግልጽ ጭስ የምትመጣበትን ቀን ተጠባበቅ፡፡(10) So wait for a day when the sky will bring forth a visible smoke,
(11) ሰዎችን የሚሸፍን (በኾነ ጭስ) ይህ አሳማሚ ቅጣት ነው፡፡(11) that will overwhelm the people. This is a painful punishment!
(12) «ጌታችን ሆይ! ከእኛ ላይ ቅጣቱን ግለጥልን፡፡ እኛ አማኞች እንኾናለንና» (ይላሉም)፡፡(12) [They will cry,] “Our Lord, remove the punishment from us; we will surely believe!”
(13) (ቅጣቱ በወረደ ጊዜ) ለእነርሱ መግገሰጽ እንዴት ይኖራቸዋል? አስረጅ መልክተኛ የመጣቸው ሲኾን (የካዱም ሲኾኑ)፡፡(13) How will they take heed, when a messenger who explained things clearly has already come to them?
(14) ከዚያም ከእርሱ የዞሩ፤ (ከሰው) «የተሰተማረ ዕብድ ነው» ያሉም ሲኾኑ፡፡(14) Then they turned away from him and said, “[He is] a madman, taught by others.”
(15) እኛ ቅጣቱን ለጥቂት ጊዜ ገላጮች ነን፡፡ እናንተ (ወደ ክህደታችሁ) በእርግጥ ተመላሾች ናችሁ፡፡(15) We shall hold the punishment back for a while, but you will surely return [to disbelief].
(16) ታላቂቱን ብርቱ አያያዝ በምንይዝበት ቀን፤ እኛ ተበቃዮች ነን፡፡(16) On the Day when We seize [them] with the greatest assault, We will surely exact retribution.
(17) ከእነርሱም በፊት የፈርዖንን ሕዝቦች በእርግጥ ሞከርን፡፡ ክቡር መልእክተኛም መጣላቸው፡፡(17) Indeed, We tested the people of Pharaoh before them, when a noble messenger came to them,
(18) «የአላህን ባሮች ወደኔ አድርሱ፡፡ እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝና፡፡(18) [saying], “Hand over to me the slaves of Allah. I am indeed a trustworthy messenger to you,
(19) «በአላህም ላይ አትኩሩ፡፡ እኔ ግልጽ የኾነን አስረጅ ያመጣሁላችሁ ነኝና (በማለት መጣላቸው)፡፡(19) and do not be arrogant towards Allah. I have certainly come to you with a clear proof.
(20) «እኔም እንዳትወግሩኝ በጌታየና በጌታችሁ ተጠብቂያለሁ፡፡(20) And I certainly seek refuge with my Lord and your Lord, lest you stone me to death.
(21) «በእኔም ባታምኑ ራቁኝ» (ተዉኝ አለ)፡፡(21) If you do not believe me, then leave me alone.”
(22) ቀጥሎም (ስለ ዛቱበት) «እነዚህ አመጸኞች ሕዝቦች ናቸው» (አጥፋቸው) ሲል ጌታውን ለመነ፡፡(22) Then he called upon his Lord, “These are a wicked people”.
(23) (ጌታው) «ባሮቼንም ይዘህ በሌሊት ኺድ፡፡ እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና፡፡(23) [Allah said], “Leave along with My slaves by night; you will surely be pursued.
(24) «ባሕሩንም የተከፈተ ኾኖ ተወው፡፡ እነርሱ የሚሰጥጠሙ ሰራዊት ናቸውና» (አለው)፡፡(24) And leave the sea parted; for they are surely an army destined to drown.”
(25) ከአትክልቶችና ከምንጮችም ብዙ ነገሮችን ተዉ፡፡(25) [Imagine] how many gardens and springs they left behind,
(26) ከአዝመራዎችም ከመልካም መቀመጫም፡፡(26) and crops and splendid mansions,
(27) በእርሷ ተደሳቾች ከነበሩባትም ድሎት (ብዙን ነገር ተዉ)፡፡(27) and luxuries they used to rejoice therein.
(28) (ነገሩ) እንደዚሁ ኾነ፡፡ ሌሎችንም ሕዝቦች አወረስናት፡፡(28) So it was; and We made another people inherit all that.
(29) ሰማይና ምድርም በእነርሱ ላይ አላለቀሱም፡፡ የሚቆዩም አልነበሩም፡፡(29) Neither the heaven nor earth wept for them, nor were they given any respite.
(30) የእስራኤልንም ልጆች አዋራጅ ከኾነ ስቃይ በእርግጥ አዳንናቸው፡፡(30) Thus did We save the Children of Israel from the humiliating punishment,
(31) ከፈርዖን፤ እርሱ የኮራ ከወሰን አላፊዎቹ ነበርና፡፡(31) from Pharaoh. He was indeed arrogant who transgressed all bounds.
(32) ከማወቅም ጋር በዓለማት ላይ በእርግጥ መረጥናቸው፡፡(32) We chose them with knowledge above all others.
(33) ከታምራቶችም በውስጡ ግልጽ የኾነ ፈተና ያለበትን ሰጠናቸው፡፡(33) And We gave them signs in which there was a clear test.
(34) እነዚህ (የመካ ከሓዲዎች) በእርግጥ ይላሉ፡-(34) Indeed, these [Makkans] say,
(35) እርሷ የፊተኛይቱ ሞታችን እንጅ አይደለችም፡፡ እኛም የምንቀሰቀስ አይደለንም፡፡(35) “There is nothing after our first death, and we will not be resurrected,
(36) እውነተኞችም እንደ ኾናችሁ አባቶቻችንን አምጡልን፡፡(36) then bring back our forefathers if you are truthful.”
(37) እነርሱ በላጮች ናቸውን ወይስ የቱብበዕ ሕዝቦችና እነዚያ ከእነርሱ በፊት የነበሩት? አጠፋናቸው፡፡ እነርሱ አመጸኞች ነበሩና፡፡(37) Are they better [in power] or the people of Tubba‘ and those who were before them? We destroyed them, for they were truly wicked.
(38) ሰማያትንና ምድርንም በሁለቱ መካከል ያለውንም ሁሉ ቀላጆች ኾነን አልፈጠርንም፡፡(38) We have not created the heavens and earth and all that is between them for amusement.
(39) ሁለቱንም በምር እንጅ አልፈጠርናቸውም፡፡ ግን አብዛኞቻቸው አያውቁም፡፡(39) We have not created them except for a true purpose, but most of them do not know.
(40) የመለያው ቀን ለሁሉም ቀጠሯቸው ነው፡፡(40) Indeed, the Day of Judgment is the time appointed for them all,
(41) ዘመድ ከዘመዱ ምንንም የማይጠቅምበት እነርሱም የማይርረዱበት ቀን ነው፡፡(41) the Day when no friend will avail another in the least, nor will they be helped,
(42) አላህ ያዘነለት ሰውና ያመነ ብቻ ሲቀር፡፡ (እርሱስ ይርረዳል)፡፡ እርሱ አሸናፊው አዛኙ ነውና፡፡(42) except those to whom Allah shows mercy. He is indeed the All-Mighty, the Most Merciful.
(43) የዘቁመ ዛፍ(43) Indeed, the tree of Zaqqūm
(44) የኀጢኣተኛው ምግብ ነው፡፡(44) will be the food of the sinful,
(45) እንደ ዘይት አተላ ነው፡፡ በሆዶች ውስጥ የሚፈላ ሲኾን፡፡(45) like molten metal that will boil in their bellies
(46) እንደ ገነፈለ ውሃ አፈላል (የሚፈላ ሲኾን)፡፡(46) like the boiling of scalding water.
(47) ያዙት፤ ወደ ገሀነም መካከልም በኀይል ጎትቱት፡፡(47) [It will be said], “Seize him and drag him into the midst of the Blazing Fire.
(48) ከዚያም «ከራሱ በላይ ከፈላ ውሃ ስቃይ አንቧቡበት፡፡»(48) Then pour over his head the torment of scalding water.”
(49) «ቅመስ፤ አንተ አሸናፊው ክብሩ ነህና» (ይባላል)፡፡(49) “Taste this. You are surely the mighty and honorable!
(50) «ይህ ያ በእርሱ ትጠራጠሩበት የነበራችሁት ነው» (ይባላሉ)፡፡(50) This is what you [all] used to doubt.”
(51) ጥንቁቆቹ በእርግጥ በጸጥተኛ መኖሪያ ውስጥ ናቸው፡፡(51) Indeed, the righteous will be in a safe place,
(52) በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡(52) in gardens and springs,
(53) ፊት ለፊት የተቅጣጩ ኾነው ከስስ ሐርና ከወፍራም ሐር ይለብሳሉ፡፡(53) wearing fine silk and heavy brocade, facing one another.
(54) (ነገሩ) እንደዚሁ ነው፤ ዓይናማዎች የኾኑን ነጫጭ ሴቶችም እናጠናዳቸዋለን፡፡(54) So it will be, and We will marry them to maidens with gorgeous eyes.
(55) በእርሷም ውስጥ የተማመኑ ኾነው፤ ከፍራፍሬ ሁሉ ያዝዛሉ፡፡(55) They will call therein for every kind of fruit, safe and secure.
(56) የፊተኛይቱን ሞት እንጅ (ዳግመኛ) በእርሷ ውስጥ ሞትን አይቀምሱም፡፡ የገሀነምንም ቅጣት (አላህ) ጠበቃቸው፡፡(56) They will not taste death therein except the first death, and He will protect them from the punishment of the Blazing Fire,
(57) ከጌታህ በኾነ ችሮታ (ጠበቃቸው)፡፡ ይህ እርሱ ታላቅ ዕድል ነው፡፡(57) as a grace from your Lord. That is the supreme triumph.
(58) (ቁርኣኑን) በቋንቋህም ያገራነው (ሕዝቦችህ) ይገነዘቡ ዘንድ ብቻ ነው፡፡(58) We have made this [Qur’an] easy in your own language, so that they may take heed.
(59) ተጠባበቅም እነርሱ ተጠባባቂዎች ናቸውና፡፡(59) Then wait; they too are waiting.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

33 – Al-Ahzaab

33 – Al-Ahzaab (1) አንተ ነቢዩ ሆይ! አላህን ፍራ፡፡ ከሓዲዎችንና መናፍቃንንም አትታዘዝ፡፡ አላህ ዐዋቂ ጥበበኛ ነውና፡፡ (1) O Prophet, fear…

113 – Al-Falaq

113 – Al-Falaq (1) በል «በተፈልቃቂው ጎህ ጌታ እጠበቃለሁ፡፡ (1) Say, “I seek refuge with the Lord of the daybreak,…

75 – Al-Qiyaama

75 – Al-Qiyaama (1) (ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡ (1) I swear by the Day of Resurrection, (2) (ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም…