Default Image
11, Dec 2023
72 – Al-Jinn

72 – Al-Jinn

(1) (ሙሐመድ ሆይ!) በል «እነሆ ከጂን የኾኑ ጭፈሮች (ቁርኣንን) አዳመጡ፡፡‹እኛ አስደናቂ የኾነን ቁርኣን ሰማንም› አሉ ማለት ወደእኔ ተወረደ፡፡(1) Say, “It has been revealed to me that a group of jinn listened [to the Qur’an,] and they said, ‘Indeed, we have heard a wondrous recitation
(2) ‹ወደ ቀጥታ መንገድ የሚመራን (ቁርአን ሰማን)፡፡ በእርሱም አመንን፡፡ በጌታችንም አንድንም አናጋራም፡፡›(2) that guides to the right way, so we have believed in it, and we will never associate anyone with our Lord.
(3) ‹እነሆም የጌታችን ክብር ላቀ፡፡ ሚስትንም ልጅንም አልያዘም፡፡›(3) And that He – our exalted and glorified Lord – has neither taken a wife nor a child;
(4) ‹እነሆም ቂላችን በአላህ ላይ ወሰን ያለፈን (ውሸት) ይናገር ነበር፡፡›(4) and that the fool among us [Satan] used to say outrageous things about Allah,
(5) ‹እኛም ሰዎችና ጋኔኖች በአላህ ላይ ውሸትን (ቃል) አይናገሩም ማለትን ጠረጠርን፡፡›(5) although we thought that humans and jinn would never tell lies about Allah.
(6) ‹እነሆም ከሰዎች የኾኑ ወንዶች በጋኔን ወንዶች ይጠበቁ ነበሩ፡፡ ኩራትንም ጨመሩዋቸው፡፡›(6) And there were some men who used to seek refuge with some jinn, but they only increased them in burden.
(7) ‹እነርሱም አላህ አንድንም አይቀሰቅስም ማለትን እንደጠረጠራችሁ ጠረጠሩ፡፡›(7) They thought, just like you [jinn] thought that Allah would never send any messenger.
(8) ‹እኛም ሰማይን (ለመድረስ) ፈለግን፡፡ ብርቱ ጠባቂዎችንና ችቦዎችንም ተሞልታ አገኘናት፡፡(8) We have sought to reach the heaven but found it filled with stern guards and flaming fire.
(9) ‹እኛም ከእርሷ (ወሬን) ለማደመጥ በመቀመጫዎች እንቀመጥ ነበርን፡፡ አሁን ግን የሚያዳምጥ ሰው ለእርሱ ተጠባባቂ ችቦን ያገኛል፡፡(9) We used to take up positions there for eavesdropping, but now anyone who eavesdrops will find a flaming fire waiting for him.
(10) ‹እኛም በምድር ውስጥ ባልሉ ሰዎች ክፉ ተሽቷል? ወይስ በእነርሱ ጌታቸው ደግን ነገር ሽቷል? ማለትን አናውቅም፡፡(10) We do not know whether evil is intended for those on earth, or their Lord intends good for them.
(11) ‹እኛም ከእኛ ውስጥ ደጎች አልሉ፡፡ ከኛም ከዚህ ሌላ የኾኑ አልሉ፡፡ የተለያዩ መንገዶች (ባለ ቤቶች) ነበርን፡፡(11) Among us are some who are righteous and some who are otherwise, for we follow divergent ways.
(12) ‹እኛም አላህን በምድር ውስጥ ፈጽሞ የማናቅተው፤ ሸሽተንም ፈጽሞ የማናመልጠው መኾናችንን አረጋገጥን፡፡(12) We have realized that we can never escape Allah on earth, nor can we ever escape Him by fleeing.
(13) ‹እኛም መሪውን በሰማን ጊዜ በርሱ አመንን፡፡ በጌታውም የሚያምን ሰው መግጎደልንም መጭጨመርንም አይፈራም፡፡(13) When we heard the guidance [of the Qur’an], we believed in it. Whoever believes in his Lord will have no fear of curtailment [from his reward] or injustice.
(14) «እኛም ከእኛ ውስጥ ሙስሊሞች አልሉ፡፡ ከእኛም ውስጥ በዳዮች አልሉ፡፡ የሰለሙም ሰዎች እነዚያ ቅንን መንገድ መረጡ፡፡»(14) Among us are some who are Muslims and some who are deviant. Those who accepted Islam have sought the true guidance,
(15) በዳዮቹማ ለገሀነም ማገዶ ኾኑ፡፡(15) but those who are deviant, they will be fuel for Hell.’”
(16) እነሆም በመንገዲቱ ላይ ቀጥ ባሉ ኖሮ ብዙ ዝናምን ባጠጣናቸው ነበር (ማለትም ተወረደልኝ)፡፡(16) “If they had remained steadfast on the right way, We would have given them abundant rain,
(17) በእርሱ ልንሞክራቸው (ባጠጣናቸው ነበር)፡፡ ከጌታውም ማስታወሻ የሚያፈገፍግ ሰው አስቸጋሪን ቅጣት ያገባዋል፡፡(17) as a test for them. But whoever turns away from the remembrance of his Lord, He will make him suffer an arduous punishment.
(18) እነሆ መስጊዶችም የአላህ ብቻ ናቸው፡፡ (በውስጣቸው) ከአላህ ጋር አንድንም አትገዙ (ማለትም)፡፡(18) The mosques are for Allah alone, so do not supplicate to anyone along with Allah.
(19) እነሆም የአላህ ባሪያ (ሙሐመድ አላህን) የሚጠራው ኾኖ በተነሳ ጊዜ (ጋኔኖች) በእርሱ ላይ ድርብርቦች ሊኾኑ ቀረቡ (ማለትም)፡፡(19) Yet when the slave of Allah stood up supplicating to Him, they swarmed around him.”
(20) «እኔ የምግገዛው ጌታየን ብቻ ነው፡፡ በእርሱም አንድንም አላጋራም» በል፡፡(20) Say [O Prophet], “I only supplicate to my Lord and I do not associate anyone with Him.”
(21) «እኔ ለእናንተ ጉዳትንም ቀጥታንም አልችልም» በላቸው፡፡(21) Say, “I have no power to harm or benefit you.”
(22) «እኔ ከአላህ (ቅጣት) አንድም አያድነኝም፡፡ ከእርሱም ሌላ መጠጊያን አላገኝም» በላቸው፡፡(22) Say, “None can ever protect me from Allah [if I should disobey Him], nor can I ever find refuge except in Him.
(23) «ከአላህ የኾነ ማድረስን መልክቶቹንም በስተቀር (አልችልም)፡፡ አላህንና መልክተኛውንም የሚያምጽ ሰው ለእርሱ የገሀነም እሳት አልለው፡፡ በውስጧ ዘላለም ዘውታሪዎች ሲኾኑ፡፡»(23) I only convey what I receive from Allah and His messages.” And whoever disobeys Allah and His Messenger will certainly be in the Fire of Hell, abiding therein forever.
(24) የሚስፈራሩበትንም ባዩ ጊዜ ረዳቱ ደካማ፣ ቁጥሩም አነስተኛ የኾነው ማን እንደኾነ በእርግጥ ያውቃሉ፡፡(24) Until when they see what they were promised, they will realize who is weaker in helpers and fewer in number.
(25) «የምትስፈራሩበት ነገር ቅርብ ወይም ጌታየ ለእርሱ የተወሰነ ጊዜን የሚያደርግለት (ሩቅ) መኾኑን አላውቅም» በላቸው፡፡(25) Say, “I do not know if what you are promised is near or my Lord has appointed a distant time for it.
(26) «(እርሱ) ሩቁን ምስጢር ዐዋቂ ነው፡፡ በምስጢሩም ላይ አንድንም አያሳውቅም፡፡»(26) [He is] the Knower of the unseen, He does not reveal His unseen to anyone,
(27) ከመልክተኛ ለወደደው ቢኾን እንጅ (ለሌላ አይገልጽም)፡፡ እርሱም ከስተፊቱም ከስተኋላውም ጠባቂዎችን ያደርግለታል፡፡(27) except the messenger whom He chooses, then He appoints angel-guards before him and behind him
(28) እነርሱ ዘንድ ባለው ነገር ዕውቀቱ የከበበና ነገሩንም ሁሉ በቁጥር ያጠቃለለ ሲኾን የጌታቸውን መልክቶች ያደረሱ መኾናቸውን ያውቅ ዘንድ (ጠባቂ ያደርጋል)፡፡(28) to ensure that the messengers fully conveyed the messages of their Lord. He encompasses in His knowledge all about them, and keeps count of all things.”

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

103 – Al-Asr

103 – Al-Asr (1) በጊዜያቱ እምላለሁ፡፡ (1) By the time, (2) ሰው ሁሉ በእርግጥ በከሳራ ውስጥ ነው፡፡ (2) man is…

28 – Al-Qasas

28 – Al-Qasas (1) ጠ.ሰ.መ (ጣ ሲን ሚም)፡፡ (1) Tā Sīn Mīm. (2) ይህቺ ገላጭ ከሆነው መጽሐፍ አንቀጾች ናት፡፡ (2) These…

44 – Ad-Dukhaan

44 – Ad-Dukhaan (1) ሐ.መ (ሓ ሚም)፡፡ (1) Hā Mīm. (2) አብራሪ በኾነው መጽሐፍ እንምላለን፡፡ (2) By the clear Book. (3)…