Default Image
19, Dec 2023
87 – Al-A’laa

87 – Al-A’laa

(1) ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡ (1) Glorify the name of your Lord, the Most High,
(2) የዚያን (ሁሉን ነገር) የፈጠረውን ያስተካከለውንም፡፡ (2) Who created and fashioned in due proportion,
(3) የዚያንም የወሰነውን፡፡ (ለተፈጠረለት ነገር) የመራውንም፡፡ (3) and Who determined [the creation] then guided them,
(4) የዚያንም ግጦሽን (ለምለም አድርጎ) ያወጣውን፡፡ (4) and Who brings forth the pasture,
(5) (ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡ (5) then makes it into withered chaff.
(6) (ቁርኣንን) በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፡፡ (6) We will teach you [the Qur’an], so you will not forget,
(7) አላህ ከሻው ነገር በስተቀር፡፡ እርሱ ግልጹን የሚሸሸገውንም ሁሉ ያውቃልና፡፡ (7) except what Allah wills, for indeed He knows what is manifest and what is hidden.
(8) ለገሪቱም (ሕግጋት) እንገጥምሃለን፡፡ (8) We will guide you to the easy way.
(9) ግሣጼይቱ ብትጠቅም (ሰዎችን) ገሥጽም፡፡ (9) So remind, if the reminder should benefit.
(10) (አላህን) የሚፈራ ሰው በእርግጥ ይገሠጻል፡፡ (10) He who fears Allah will take heed,
(11) መናጢውም ይርቃታል፡፡ (11) but the wretched will avoid it,
(12) ያ ታላቂቱን እሳት የሚገባው፡፡ (12) who will enter the Great Fire,
(13) ከዚያም በእርሷ ውስጥ አይሞትም ሕያውም አይኾንም፡፡ (13) wherein he will neither die nor live.
(14) የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፡፡ (14) Indeed, he who purifies himself will attain success,
(15) የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ፡፡ (15) and remembers his Lord’s Name and prays.
(16) ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ትመርጣላችሁ፡፡ (16) But you prefer the life of this world,
(17) መጨረሻይቱ (ሕይወት) በላጭ ሁል ጊዜ ዘውታሪም ስትኾን፡፡ (17) even though the Hereafter is better and more lasting.
(18) ይህ በፊተኞቹ መጻሕፍት ውስጥ ያልለ ነው፡፡ (18) Indeed, this was in the earlier Scriptures,
(19) በኢብራሂምና በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ፡፡ (19) the Scriptures of Abraham and Moses.

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

ሱረቱል አል-በቀራህ አማርኛ ቅዱስ ቁርአን ምዕራፍ 2 Amharic Quran

ሱረቱል አል-በቀራህ አማርኛ ቅዱስ ቁርአን ምዕራፍ 2 Amharic Quran بِسۡمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحۡمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ Bismillah hir rahman nir raheem الم  [1] (1) አ.ለ.መ    (1)…

ሱረቱል አል ዒምራን አማርኛ ቁርአን / Al-Imraan

ሱረቱል አል ዒምራን አማርኛ ቁርአን / Al-Imraan الم [1] Alif-Laam-Meeem (1) አ.ለ.መ (አሊፍ ላም ሚም)፤ (1) Alif Lām Mīm. اللَّهُ…

90 – Al-Balad

90 – Al-Balad (1) በዚህ አገር (በመካ) እምላለሁ፡፡ (1) I do swear by this city [of Makkah] – (2) አንተ በዚህ አገር ሰፋሪ ስትኾን፡፡…