79 – An-Naazi’aat
79 – An-Naazi’aat
| (1) በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤ | (1) By those who pull out [evil souls] harshly, |
| (2) በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤ | (2) and by those who draw out [good souls] gently, |
| (3) መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤ | (3) and by those who glide swiftly, |
| (4) መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤ | (4) and those who overtake one another as in a race, |
| (5) ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡ | (5) and those who carry out the command [of Allah], |
| (6) ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤ | (6) on the Day when the earth convulses [by the first Blast], |
| (7) ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡ | (7) followed by the second Blast, |
| (8) በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡ | (8) hearts will be pounding on that Day, |
| (9) ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡ | (9) and their eyes will be downcast. |
| (10) «እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡ | (10) They say, “Will we be brought back to life, |
| (11) «የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)» | (11) after we have turned into decayed bones?” |
| (12) «ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡ | (12) They say, “Then that would surely be a losing return!” |
| (13) እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ | (13) It will only be a single Blast, |
| (14) ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡ | (14) then they will immediately be above the ground. |
| (15) የሙሳ ወሬ መጣልህን? | (15) Has there come to you the story of Moses, |
| (16) ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤ | (16) when his Lord called out to him at the sacred valley of Tuwa? |
| (17) ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡ | (17) [Saying,] “Go to Pharaoh, for he has transgressed all bounds”. |
| (18) በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?» | (18) And say: ‘Are you willing to be purified, |
| (19) «ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡ | (19) and I will guide you to your Lord so that you may fear Him?’” |
| (20) ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡ | (20) Then Moses showed him the greatest sign. |
| (21) አስተባበለም፤ አመጸም፡፡ | (21) But Pharaoh denied it and disobeyed. |
| (22) ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡ | (22) Then he turned back striving to plot. |
| (23) (ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡ | (23) He gathered [his people] and proclaimed, |
| (24) አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡» | (24) saying, “I am your lord, the most high.” |
| (25) አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡ | (25) So Allah seized him for an exemplary punishment in this life and in the Hereafter. |
| (26) በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡ | (26) Indeed, there is a lesson in this for those who fear Allah. |
| (27) ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡ | (27) Are you more difficult to create or the heaven that He built? |
| (28) ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡ | (28) He raised it high and proportioned it, |
| (29) ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡ | (29) and darkened its night and brought forth its daylight. |
| (30) ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡ | (30) And thereafter He spread out the earth, |
| (31) ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡ | (31) brought forth from it its water and its pasture, |
| (32) ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡ | (32) and set the mountains firmly, |
| (33) ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡ | (33) as a provision for you and your grazing livestock. |
| (34) ታላቂቱም መዐት በመጣች ጊዜ፣ | (34) But when the Supreme Calamity comes, |
| (35) ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣ | (35) on that Day man will remember all what he did, |
| (36) ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣ | (36) and the Blazing Fire will be exposed for all to see. |
| (37) የካደ ሰውማ፣ | (37) As for those who transgressed, |
| (38) ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣ | (38) and preferred the life of this world, |
| (39) ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡ | (39) the Blazing Fire will be their abode. |
| (40) በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ | (40) But those who feared standing before their Lord and restrained themselves from evil desires, |
| (41) ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡ | (41) Paradise will surely be their abode. |
| (42) «ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡ | (42) They ask you concerning the Hour, “When will it be?” |
| (43) አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ? | (43) How could you possibly mention that? |
| (44) (የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡ | (44) Its knowledge rests only with your Lord. |
| (45) አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡ | (45) You are only a warner for those who fear it. |
| (46) እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡ | (46) On the Day when they see it, it will be as if they had remained [in this world] no more than an evening or a morning. |
