Default Image
11, Dec 2023
79 – An-Naazi’aat

79 – An-Naazi’aat

(1) በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤(1) By those who pull out [evil souls] harshly,
(2) በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤(2) and by those who draw out [good souls] gently,
(3) መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤(3) and by those who glide swiftly,
(4) መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤(4) and those who overtake one another as in a race,
(5) ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡(5) and those who carry out the command [of Allah],
(6) ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤(6) on the Day when the earth convulses [by the first Blast],
(7) ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡(7) followed by the second Blast,
(8) በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡(8) hearts will be pounding on that Day,
(9) ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡(9) and their eyes will be downcast.
(10) «እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡(10) They say, “Will we be brought back to life,
(11) «የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»(11) after we have turned into decayed bones?”
(12) «ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡(12) They say, “Then that would surely be a losing return!”
(13) እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡(13) It will only be a single Blast,
(14) ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡(14) then they will immediately be above the ground.
(15) የሙሳ ወሬ መጣልህን?(15) Has there come to you the story of Moses,
(16) ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤(16) when his Lord called out to him at the sacred valley of Tuwa?
(17) ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡(17) [Saying,] “Go to Pharaoh, for he has transgressed all bounds”.
(18) በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»(18) And say: ‘Are you willing to be purified,
(19) «ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡(19) and I will guide you to your Lord so that you may fear Him?’”
(20) ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡(20) Then Moses showed him the greatest sign.
(21) አስተባበለም፤ አመጸም፡፡(21) But Pharaoh denied it and disobeyed.
(22) ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡(22) Then he turned back striving to plot.
(23) (ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡(23) He gathered [his people] and proclaimed,
(24) አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»(24) saying, “I am your lord, the most high.”
(25) አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡(25) So Allah seized him for an exemplary punishment in this life and in the Hereafter.
(26) በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡(26) Indeed, there is a lesson in this for those who fear Allah.
(27) ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡(27) Are you more difficult to create or the heaven that He built?
(28) ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡(28) He raised it high and proportioned it,
(29) ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡(29) and darkened its night and brought forth its daylight.
(30) ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡(30) And thereafter He spread out the earth,
(31) ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡(31) brought forth from it its water and its pasture,
(32) ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡(32) and set the mountains firmly,
(33) ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡(33) as a provision for you and your grazing livestock.
(34) ታላቂቱም መዐት በመጣች ጊዜ፣(34) But when the Supreme Calamity comes,
(35) ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣(35) on that Day man will remember all what he did,
(36) ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣(36) and the Blazing Fire will be exposed for all to see.
(37) የካደ ሰውማ፣(37) As for those who transgressed,
(38) ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣(38) and preferred the life of this world,
(39) ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡(39) the Blazing Fire will be their abode.
(40) በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ(40) But those who feared standing before their Lord and restrained themselves from evil desires,
(41) ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡(41) Paradise will surely be their abode.
(42) «ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡(42) They ask you concerning the Hour, “When will it be?”
(43) አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ?(43) How could you possibly mention that?
(44) (የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡(44) Its knowledge rests only with your Lord.
(45) አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡(45) You are only a warner for those who fear it.
(46) እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡(46) On the Day when they see it, it will be as if they had remained [in this world] no more than an evening or a morning.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

59 – Al-Hashr

59 – Al-Hashr (1) በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለው ሁሉ ለአላህ አሞገሰ፡፡ እርሱም አሸናፊው ጥበበኛው ነው፡፡ (1) All that is in…

64 – At-Taghaabun

64 – At-Taghaabun (1) በሰማያት ውስጥ ያለው በምድርም ውስጥ ያለው ሁሉ ለአላህ ያሞግሳል፡፡ ንግሥናው የእርሱ ብቻ ነው፡፡ ምስጋናም ለእርሱ ነው፡፡…

52 – At-Tur

52 – At-Tur (1) በጡር (ጋራ) እምላለሁ፡፡ (1) By the mount of Tūr, (2) በተጻፈው መጽሐፍም፡፡ (2) and by the Book inscribed…