Default Image
11, Dec 2023
69 – Al-Haaqqa

69 – Al-Haaqqa

(1) እውነትን አረጋጋጪቱ (ትንሣኤ)፡፡(1) The Inevitable Hour!
(2) አረጋጋጪቱም (እርሷ) ምንድን ናት!(2) What is the Inevitable Hour?
(3) አረጋጋጪቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?(3) How do you know what the Inevitable Hour is?
(4) ሰሙድና ዓድ በቆርቋሪይቱ (ትንሣኤ) አስተባበሉ፡፡(4) Thamūd and ‘Ād denied the striking calamity of the Hour.
(5) ሠሙድማ ወሰን በሌላት ጩኸት ተጠፋ፤ (ተወደሙ)፡፡(5) As for Thamūd, they were destroyed by a dreadful blast.
(6) ዓድማ በኀይል በምትንሻሻ ብርቱ ነፋስ ተጠፉ፡፡(6) And as for ‘Ād, they were destroyed by a furious windstorm
(7) ተከታታይ በኾኑ ሰባት ሌሊቶችና ስምንት መዓልቶች ውስጥ በእነርሱ ላይ ለቀቃት፡፡ ሕዝቦቹንም፤ በውስጧ የተጣሉ ኾነው ልክ ክፍት የኾኑ የዘንባባ ግንዶች መስለው ታያቸዋለህ፡፡(7) which He unleashed against them for seven successive nights and eight days, so you would see the people lying dead as if they were hollow trunks of palm trees.
(8) ለእነርሱም ቀሪን ታያለህን?(8) Do you see any trace of them now?
(9) ፈርዖን ከበፊቱ የነበሩትም ሰዎች ተገልባጮቹም (ከተሞች) በኀጢአት (ሥራዎች) መጡ፡፡(9) Also Pharaoh and those who came before him, and the overturned cities [of Lot] committed grave sin,
(10) የጌታቸውንም መልእክተኛ ትዕዛዝ ጣሱ፡፡ የበረታችንም አያያዝ ያዛቸው፡፡(10) each disobeying the messenger of their Lord, so He seized them with a severe punishment.
(11) እኛ ውሃው ባየለ ጊዜ በተንሻላይቱ ታንኳ ውስጥ ጫንናችሁ፡፡(11) Indeed, when the floodwater overflowed, We carried you [O humans] in the sailing Ark,
(12) ለእናንተ መገሰጫ ልናደርጋት አጥኒ የኾነችም ጆሮ ታጠናት ዘንድ፡፡(12) so that We might make it a reminder for you, and that attentive ears may take heed.
(13) በቀንዱም አንዲት መንነፋት በተነፋች ጊዜ፡፡(13) Then when the Trumpet is blown with a single blast,
(14) ምድርና ጋራዎችም (ከስፍራቸው) በተነሱና አንዲትን መሰባበር በተሰባበሩ ጊዜ፡፡(14) and the earth and mountains are lifted up and crushed with a single blow,
(15) በዚያ ቀን ኋኝቱ (ትንሣኤ) ትኾናለች፡፡(15) on that Day the Inevitable Event will occur.
(16) ሰማይም ትቀደዳለች፡፡ ስለዚህ እርሷ በዚያ ቀን ደካማ ናት፡፡(16) And the sky will split asunder and will be frail on that day,
(17) መላእክትም በየጫፎችዋ ላይ ይኾናሉ፡፡ የጌታህንም ዐርሽ በዚያ ቀን ስምንት መላእክት ከበላያቸው ይሸከማሉ፡፡(17) with the angels on all its sides, and on that Day, eight [mighty angels] will bear the Throne of your Lord above them.
(18) በዚያ ቀን ከእናንተ ተደባቂ (ነገሮች) የማይደበቁ ሲኾኑ ትቅቀረባላችሁ፡፡(18) On that day, you will be brought forth [before Allah], and none of your secrets will remain hidden.
(19) መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ (ለጓደኞቹ) «እንኩ፤ መጽሐፌን አንብቡ» ይላል፡፡(19) As for the one who is given his Record in his right hand, he will say, “Here is my Record, read it!
(20) «እኔ ምርመራየን የምገናኝ መኾኔን አረጋገጥኩ፤» (ተዘጋጀሁም ይላል)፡፡(20) I was sure that I would meet my reckoning.”
(21) እርሱም በተወደደች ኑሮ ውሰጥ ይኾናል፡፡(21) So he will be in a pleasant life,
(22) በከፍተኛይቱ ገነት ውስጥ፡፡(22) in a lofty garden,
(23) ፍሬዎችዋ ቅርቦች የኾኑ፡፡(23) with clustered fruit within his reach.
(24) በአለፉት ቀናት ውስጥ (በምድረ ዓለም) ባስቀደማችሁት ምክንያት ብሉ፤ ጠጡም፤ (ይባላሉ)፡፡(24) [They will be told,] “Eat and drink joyfully for what you did in the days gone by.”
(25) መጽሐፉንም በግራው የተሰጠማ «ዋ ጥፋቴ! ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ» ይላል፡፡(25) As for the one who is given his Record in his left hand, he will say, “Would that I had not been given my Record,
(26) «ምርመራየንም ምን እንደኾነ ባላወቅኩ፡፡(26) nor had I known anything of my reckoning!
(27) «እርሷ (ሞት ሕይወቴን) ምነው ፈጻሚ በኾነች፡፡(27) Would that it [death] had been the end of me!
(28) «ገንዘቤ ከእኔ ምንንም አላብቃቃኝ፤ (አልጠቀመኝም)፡፡(28) My wealth has been of no avail to me.
(29) «ኀይሌ ከእኔ ላይ ጠፋ» (ይላል)፡፡(29) My authority has vanished.”
(30) «ያዙት፤ እሰሩትም፡፡(30) [It will be said,] “Seize him and shackle him,
(31) «ከዚያም በእሳት ውሰጥ አግቡት፡፡(31) then make him burn in the Blazing Fire,
(32) «ከዚያም ርዝመቷ ሰባ ክንድ በኾነች ሰንሰለት ውስጥ አግቡት፡፡»(32) then tie him up with a chain of seventy cubits long.
(33) እርሱ ታላቅ በኾነው አላህ አያምንም ነበርና፡፡(33) For he did not believe in Allah, the Most Great,
(34) ድኾችንም በማብላት ላይ አያግባባም ነበርና፡፡(34) nor did he encourage feeding the needy.
(35) ለእርሱም ዛሬ እዚህ ዘመድ የለውም፡፡(35) So Today he will have no close friend here,
(36) ምግብም ከእሳት ሰዎች ቁስል እጣቢ (እዥ) በስተቀር የለውም፡፡(36) nor any food except the discharge of wounds,
(37) ኀጢኣተኞች እንጅ ሌላ አይበላውም፤ (ይባላል)፡፡(37) none will eat it except the sinners.”
(38) በምታዩትም ነገር እምላለሁ፡፡(38) I swear by what you can see.
(39) በማታዩትም ነገር፡፡(39) and what you cannot see!
(40) እርሱ (ቁርኣን) የተከበረ መልክተኛ ቃል ነው፡፡(40) Indeed, this is the word of a noble Messenger,
(41) እርሱም የባለቅኔ ቃል (ግጥም) አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታምናላችሁ፡፡(41) and it is not the word of a poet; little do you believe!
(42) የጠንቋይም ቃል አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታስታውሳላችሁ፡፡(42) Nor is it the word of a soothsayer; little do you take heed!
(43) ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡(43) It is a revelation from the Lord of the worlds.
(44) በእኛ ላይም ከፊልን ቃላት (ያላልነውን) በቀጠፈ ኖሮ፤(44) If he had falsely attributed something to Us,
(45) በኀይል በያዝነው ነበር፡፡(45) We would have surely seized him by the right hand,
(46) ከዚያም ከእርሱ የልቡን ሥር (የተንጠለጠለበትን ጅማት) በቆረጥን ነበር፡፡(46) then severed his aorta,
(47) ከእናንተም ውስጥ ከእርሱ ላይ ከልካዮች ምንም አይኖሩም፡፡(47) and none of you could have rescued him.
(48) እርሱም (ቁርኣን) ለጥንቁቆቹ መገሠጫ ነው፡፡(48) This [Qur’an] is indeed a reminder for those who are righteous.
(49) እኛም ከእናንተ ውስጥ አስተባባዮች መኖራቸውን በእርግጥ እናውቃለን፡፡(49) And We surely know that some of you will be deniers,
(50) እርሱም (ቁርኣን) በከሓዲዎቹ ላይ ጸጸት ነው፡፡(50) and it will certainly be a source of regret for the disbelievers.
(51) እርሱም የተረጋገጠ እውነት ነው፡፡(51) And this is indeed the absolute truth.
(52) የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡(52) So glorify the name of your Lord, the Most Great.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

55 – Ar-Rahmaan

55 – Ar-Rahmaan (1) አል-ረሕማን፤ (1) The Most Compassionate, (2) ቁርኣንን አስተማረ፡፡ (2) has taught the Qur’an, (3) ሰውን ፈጠረ፡፡…

77 – Al-Mursalaat

77 – Al-Mursalaat (1) ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣ (1) By those [winds] sent forth in succession, (2) በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣ (2) those…

53 – An-Najm

53 – An-Najm (1) በኮከብ እምላለሁ በወደቀ (በገባ) ጊዜ፡፡ (1) By the star when it sets, (2) ነቢያችሁ (ሙሐመድ) አልተሳሳተም፤ አልጠመመምም፡፡ (2) Your companion [the…