Default Image
21, Nov 2023
20 – Taa-Haa 
(1) ጠ.ሀ. (ጣ ሃ)(1) Tā Ha
(2) ቁርኣንን ባንተ ላይ እንድትቸገር አላወረድንም፡፡(2) We have not sent down the Qur’an to you [O Prophet] to cause you distress,
(3) ግን አላህን ለሚፈራ ሰው መገሰጫ ይኾን ዘንድ (አወረድነው)፡፡(3) but as a reminder for those who fear Allah.
(4) ምድርንና የላይኛዎቹን ሰማያት ከፈጠረ አምላክ ተወረደ፡፡(4) A revelation from the One Who created the earth and the high heavens.
(5) (እርሱ) አልረሕማን ነው በዐርሹ ላይ (ለሱ ክብር በሚስማማ መልኩ) ተደላደለ፡፡(5) The Most Compassionate rose over the Throne.
(6) በሰማያት ያለው፣ በምድርም ያለው፣ በመካከላቸውም ያለው፣ ከዐፈር በታችም ያለው ሁሉ የርሱ ብቻ ነው፡፡(6) To Him belongs all that is in the heavens and all that is on earth, and all that is between them, and all that is beneath the soil.
(7) በንግግር ብትጮህ (አላህ ከጩኸቱ የተብቃቃ ነው)፡፡ እርሱ ምስጢርን በጣም የተደበቀንም ያውቃልና፡፡(7) Whether you speak loudly [or not], He surely knows what is secret and what is even more hidden.
(8) አላህ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ ለእርሱ መልካሞች የኾኑ ስሞች አልሉት፡፡(8) Allah – none has the right to be worshiped except Him. He has the Most Beautiful Names.
(9) የሙሳም ወሬ በእርግጥ መጥቶሃል፡፡(9) Has there come to you the story of Moses?
(10) እሳትን ባየና ለቤተሰቦቹ፡- (እዚህ) «ቆዩ፤ እኔ እሳትን አየሁ፡፡ ከእርሷ ችቦን ላመጣላችሁ፤ ወይም እሳቲቱ ዘንድ መሪን ላገኝ እከጅላለሁ» ባለጊዜ (አስታውስ)፡፡(10) When he saw a fire, he said to his family, “Stay here. I have spotted a fire; I may bring you a flaming brand from it, or find some guidance at the fire.”
(11) በመጣትም ጊዜ «ሙሳ ሆይ» በማለት ተጠራ፡፡(11) When he came to it, he was called, “O Moses,
(12) «እኔ ጌታህ እኔ ነኝ መጫሚያዎችህንም አውልቅ፡፡ አንተ በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ ነህና፡፡(12) Indeed, I am your Lord, so take off your shoes; you are in the sacred valley of Tuwā.
(13) «እኔም መረጥኩህ፤ የሚወረድልህንም ነገር አዳምጥ፡፡(13) I have chosen you, so listen to what is being revealed:
(14) «እኔ አላህ እኔ ነኝ ያለ እኔ አምላክ የለምና ተገዛኝ፡፡ ሶላትንም (በእርሷ) እኔን ለማውሳት ስገድ፡፡(14) ‘Indeed, I am Allah; none has the right to be worshiped except Me, so worship Me and establish prayer to remember me.
(15) «ሰዓቲቱ በእርግጥ መጪናት፡፡ ልደብቃት እቃረባለሁ፡፡ ነፍስ ሁሉ በምትሠራው ነገር ትመነዳ ዘንድ (መጭ ናት)፡፡(15) The Hour is certainly coming, but I almost keep it hidden, so that every soul will be recompensed for what it strives.
(16) «በእርሷ የማያምነውና ዝንባሌውን የተከተለውም ሰው ከእርሷ አያግድህ ትጠፋለህና፡፤(16) So do not let those who disbelieve in it and follow their desires distract you from it, or you will perish.’”
(17) «ሙሳ ሆይ! ይህችም በቀኝ እጅህ ያለችው ምንድን ናት» (ተባለ)፡፡(17) What is that in your right hand, O Moses?”
(18) «እርሷ በትሬ ናት፡፡ በእርሷ ላይ እደገፍባታለሁ፣ በእርሷም ለፍየሎቼ ቅጠልን አረግፍባታለሁ፣ ለእኔም በእርሷ ሌሎች ጉዳዮች አሉኝ» አለ፡፡(18) He said, “It is my staff. I lean on it and beat down leaves with it for my sheep, and I have other uses for it.”
(19) (አላህም) «ሙሳ ሆይ! ጣላት» አለው፡፡(19) Allah said, “Throw it down, O Moses!”
(20) ጣላትም፡፡ ወዲያውም እርሷ የምትሮጥ እባብ ኾነች፡፡(20) He threw it down, and it suddenly became a slithering snake.
(21) «ያዛት፤ አትፍራም፡፡ ወደ መጀመሪያ ጠባይዋ እንመልሳታለን» አለው፡፡(21) Allah said, “Pick it up, and have no fear. We will restore it to its former state.
(22) «እጅህንም ወደ ብብትህ አግባ፡፡ ሌላ ተዓምር ስትኾን ያለነውር ነጭ ኾና ትወጣለችና፡፡(22) Put your hand under your armpit; it will come out shining white without blemish, as another sign,
(23) «ከተዓምራቶቻችን ታላቋን እናሳይህ ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡(23) so that We may show you some of Our greatest signs.
(24) «ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡»(24) Go to Pharaoh, for he has transgressed all bounds.”
(25) (ሙሳም) አለ «ጌታዬ ሆይ! ልቤን አስፋልኝ፡፡(25) He said, “My Lord, reassure my heart for me,
(26) «ነገሬንም ለእኔ አግራልኝ፡፡(26) and ease my task for me,
(27) «ከምላሴም መኮላተፍን ፍታልኝ፡፡(27) and loosen the knot from my tongue,
(28) «ንግግሬን ያውቃሉና፡፡(28) so that they may understand my speech.
(29) «ከቤተሰቦቼም ለእኔ ረዳትን አድርግልኝ፡፡(29) And appoint for me a helper from my family,
(30) «ሃሩንን ወንድሜን፡፡(30) Aaron, my brother.
(31) «ኅይሌን በእርሱ አበርታልኝ፡፡(31) Increase my strength through him,
(32) «በነገሬም አጋራው፡፡(32) and let him share my task,
(33) «በብዙ እናጠራህ ዘንድ፡፡(33) so that we may glorify You much,
(34) «በብዙም እንድናወሳህ፡፡(34) and remember You much.
(35) «አንተ በእኛ ነገር ዐዋቂ ነህና፡፡»(35) For indeed You are All-Watchful over us.”
(36) (አላህም) አለ «ሙሳ ሆይ! ልመናህን በእርግጥ ተሰጠህ፡፡(36) Allah said, “You are granted your request, O Moses.
(37) «በሌላም ጊዜ ባንተ ላይ በእርግጥ ለግሰናል፡፡(37) And We had already conferred favor upon you before,
(38) «ወደናትህ በልብ የሚፈስን ነገር ባሳወቅን ጊዜ፡፡(38) when We inspired your mother, saying,
(39) «(ሕፃኑን) በሳጥኑ ውስጥ ጣይው፡፡ እርሱንም (ሳጥኑን) በባሕር ላይ ጣይው፡፡ ባሕሩም በዳርቻው ይጣለው፡፡ ለእኔ ጠላት ለእርሱም ጠላት የኾነ ሰው ይይዘዋልና በማለት (ባሳወቅን ጊዜ ለገስንልህ)፡፡ ባንተ ላይም ከእኔ የኾነን መወደድ ጣልኩብህ፡፡ (ልትወደድና) በእኔም ጥበቃ ታድግ ዘንድ፡፡(39) ‘Put him into the casket, then cast it into the river. The river will carry it to the shore, and he will be picked up by one who is an enemy to Me and enemy to him.’ I bestowed upon you love from Myself so that you would be brought up under My [watchful] Eye.
(40) «እኅትህም በምትኼድና የሚያሳድገውን ሰው ላመላክታችሁን በምትል ጊዜ (መወደድን ጣልኩብህ)፡፡ ወደ እናትህም ዓይንዋ እንዲረጋ (እርሷ) እንዳታዝንም መለስንህ፡፡ ነፍስንም ገደልክ፡፡ ከጭንቅም አዳንንህ፡፡ ፈተናዎችንም ፈተንህ፡፡ በመድየን ቤተሰቦችም ውስጥ (ብዙ) ዓመታትን ተቀመጥክ፡፡ ከዚያም ሙሳ ሆይ! በተወሰነ ጊዜ ላይ መጣህ፡፡(40) When your sister was going along and said, ‘Shall I show you someone who will nurse him?’ Thus We brought you back to your mother, so that she may rejoice and not grieve. Then you killed a man [by mistake], but We saved you from distress, and We put you through several trials. You stayed among the people of Midian for several years, then you came [here] at a destined time, O Moses.
(41) «ለነፍሴም (በመልእክቴ) መረጥኩህ፡፡(41) I have chosen you for Myself.
(42) «አንተም ወንድምህም በተዓምራቶቼ ኺዱ፡፡ እኔንም ከማውሳት አትቦዝኑ፡፡(42) Go forth, you and your brother, with My signs and do not slacken in remembering Me.
(43) «ወደ ፈርዖን ኺዱ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡(43) Go, both of you, to Pharaoh, for he has certainly transgressed all bounds.
(44) «እርሱም ይገሰጽ ወይም ይፈራ ዘንድ፤ ለእርሱ ልዝብን ቃል ተናገሩት፡፡»(44) But speak to him gently, so that he may take heed or fear Allah.”
(45) «ጌታችን ሆይ! እኛ በእኛ ላይ ክፋት በመሥራት መቸኮሉን ወይም ኩራትን መጨመሩን እንፈራለን» አሉ፡፡(45) They said, “Our Lord, we fear that he may hasten to punish us or transgress all bounds.”
(46) (አላህም) አለ «አትፍሩ፡፡ እኔ በእርግጥ ከእናንተ ጋር ነኝና፡፡ እሰማለሁ፤ አያለሁም፡፡(46) He said, “Do not be afraid; I am with you both, hearing and seeing.
(47) «ወደርሱም ኺዱ፤ በሉትም፡- ‹እኛ የጌታህ መልክተኞች ነን፡፡› የእስራኤልንም ልጆች ከኛ ጋር ልቀቅ፡፡ አታሰቃያቸውም፡፡ ከጌታህ በኾነው ተዓምር በእርግጥ መጥተንሃልና፡፡ ሰላምም ቀጥታን በተከተለ ሰው ላይ ይኹን፡፡(47) So go to him and say, ‘We are both messengers from your Lord, so let the Children of Israel go with us and do not oppress them. We have come to you with a sign from your Lord; and peace be upon he who follows the true guidance.
(48) «እኛ ቅጣቱ ባስተባበለና እምቢ ባለ ሰው ላይ ነው ማለት በእርግጥ ተወረደልን፡፡»(48) It has been revealed to us that the punishment awaits those who reject [the truth] and turn away.’”
(49) (ፈርዖንም) «ሙሳ ሆይ! ጌታችሁ ማነው» አለ፡፡(49) Pharaoh said, “So who is the Lord of you two, O Moses?”
(50) «ጌታችን ያ ለፍጥረቱ ነገርን ሁሉ (የሚያስፈልገውን) የሰጠ ከዚያም የመራው ነው» አለው፡፡(50) He said, “Our Lord is the One Who gave everything its form then guided it.”
(51) (ፈርዖንም) «የመጀመሪያይቱ ዘመናት ሕዝቦች ኹኔታ ምንድን ነው» አለ፡፡(51) Pharaoh said, “Then what about the former [disbelieving] nations?”
(52) (ሙሳም) «ዕውቀትዋ እጌታዬ ዘንድ በመጽሐፍ የተመዘገበ ነው፡፡ ጌታዬ አይሳሳትም አይረሳምም» አለው፡፡(52) He said, “Its knowledge is with my Lord in a Record. My Lord never errs, nor does He forget.”
(53) (እርሱ) ያ ምድርን ለእናንተ ምንጣፍ ያደረገላችሁ፣ በእርሷም ውስጥ ለእናንተ መንገድን ያገራላችሁ፣ ውሃንም ከሰማይ ያወረደ ነው (አለ)፡፡ በርሱም ከተለያየ በቃይ ዓይነቶችን አወጣንላችሁ፡፡(53) It is He Who spread out the earth for you and made therein pathways for you, and sent down rain from the sky; and We brought forth thereby various types of plants.
(54) ብሉ እንስሳዎቻችሁንም አግጡ፤ (ባዮች ኾነን አወጣንላችሁ)፡፡ በዚህ ውስጥ ለአእምሮ ባለቤቶች በእርግጥ ተዓምራት አለበት፡፡(54) Eat and graze your livestock. Indeed, there are signs in this for people of sound intellect.
(55) ከእርሷ (ከምድር) ፈጠርናችሁ፡፡ በእርሷም ውስጥ እንመልሳችኋለን፡፡ ከእርሷም በሌላ ጊዜ እናወጣችኋለን፡፡(55) From this [earth] We created you, and to it We will return you, and from it We will raise you once again.
(56) ተዓምራቶቻችንንም ሁሏንም (ለፈርዖን) በእርግጥ አሳየነው፡፡ አስተባበለም፡፡ እምቢም አለ፡፡(56) We showed Pharaoh all Our signs, but he rejected them and refused to believe.
(57) «ከምድራችን በድግምትህ ልታወጣን መጣህብን ሙሳ ሆይ!» አለ፡፡(57) He said, “Have you come to drive us out of our land with your magic, O Moses?
(58) «መሰሉንም ድግምት እናመጣብሃለን፡፡ በእኛና ባንተም መካከል እኛም አንተም የማንጥሰው የኾነ ቀጠሮን በመካከለኛ ስፍራ አድርግልን» አለ፡፡(58) We will surely bring you similar magic. So appoint a day between us that neither you nor we will fail to keep, in a convenient place.”
(59) «ቀጠሯችሁ በማጌጫው ቀን ሰዎቹም በረፋድ በሚሰበሰቡበት ነው» አለ፡፡(59) Moses said, “Your appointment is the festival day; let the people be gathered at forenoon.”
(60) ፈርዖንም ዞረ፡፡ ተንኮሉንም ሰበሰበ፡፡ ከዚያም መጣ፡፡(60) So Pharaoh went away and put together his scheme, then came forth.
(61) ሙሳ ለእነሱ አላቸው «ወዮላችሁ በአላህ ላይ ውሸትን አትቅጠፉ፡፡ በቅጣት ያጠፋችኋልና፡፡ የቀጠፈም ሰው በእርግጥ አፈረ፡፡»(61) Moses said to them, “Woe to you, do not fabricate lies against Allah, lest He exterminate you with a punishment. Those who fabricate lies are bound to fail.”
(62) (ድግምተኞቹ) በመካከላቸውም ነገራቸውን ተጨቃጨቁ፡፡ ውይይትንም ደበቁ፡፡(62) Then they disputed the matter among themselves, and kept their talk private.
(63) «እነዚህ በእርግጥ ደጋሚዎች ናቸው፡፡ ከምድራችሁ በድግምታቸው ሊያወጧችሁ በላጪቱንም መንገዳችሁን ሊያስወግዱባችሁ ይሻሉ» አሉ፡፡(63) They said, “These two are merely magicians who want to drive you out of your land with their magic and destroy your exemplary way of life.
(64) «ተንኮላችሁንም አጠንክሩ፡፡ ከዚያም ተሰልፋችሁ ኑ፡፡ ዛሬ ያሸነፈም ሰው ምኞቱን አገኘ» (ተባባሉ)፡፡(64) So gather your scheme, then line up in a row. Whoever prevails today is indeed the victor.”
(65) «ሙሳ ሆይ! ወይ ትጥላለህ ወይም በመጀመሪያ የምንጥል እንኾናለን» (ምረጥ) አሉ፡፡(65) They said, “O Moses, either you throw or shall we be the first to throw!”
(66) «አይደለም ጣሉ» አላቸው፡፡ ወዲያውም ገመዶቻቸውና ዘንጎቻቸው ከድግምታቸው የተነሳ እነርሱ የሚሮጡ (እባቦች) ኾነው ወደርሱ ተመለሱ፡፡(66) He said, “No; you throw first.” Suddenly their ropes and staffs appeared to him, owing to their magic, as if they were slithering.
(67) ሙሳም በነፍሱ ውስጥ ፍርሃትን አሳደረ፡፡(67) Then Moses sensed fear within himself.
(68) «አትፍራ አንተ የበላዩ አንተ ነህና» አልነው፡፡(68) We said, “Do not be afraid; it is you who will prevail.
(69) «በቀኝ እጅህ ያለቸውንም በትር ጣል፡፡ ያንን የሠሩትን ትውጣለችና፡፡ ያ የሠሩት ሁሉ የድግምተኛ ተንኮል ነውና፡፡ ድግምተኛም በመጣበት ስፍራ ሁሉ አይቀናውም» (አልን)፡፡(69) Throw what is in your right hand; it will swallow up what they have contrived. They have only contrived a magic trick, and the magician will never prosper, wherever he goes.”
(70) ድግምተኞቹም ሰጋጆች ኾነው ወደቁ፡፡ «በሃሩንና በሙሳ ጌታ አመንን» አሉ፡፡(70) So the magicians fell down in prostration, saying, “We believe in the Lord of Aaron and Moses.”
(71) (ፈርዖንም) «ለእናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት ለእርሱ አመናችሁን እርሱ በእርግጥ ያ ድግምትን ያስተማራችሁ ትልቃችሁ ነው፡፡ እጆቻችሁንና እግሮቻችሁን በማናጋት (ግራናቀኝን በማፈራረቅ) እቆራርጣችኋለሁ፡፡ በዘምባባም ግንዶች ለይ እሰቅላችኋለሁ፡፡ ማንኛችንም ቅጣቱ በጣም ብርቱ የሚቆይም መኾኑን ታውቃላችሁ» አላቸው፡፡(71) Pharaoh said, “How dare you believe in him before I give you permission! He must be your master who taught you magic! I will surely cut off your hands and feet on opposite sides, and I will crucify you on the trunks of palm trees; you will surely know whose punishment is more severe and more lasting!”
(72) ከመጡልን ታምራቶች ከዚያም ከፈጠረን(አምላክ) ፈጽሞ አንመርጥህም፤ አንተም የምትፈርደውን ፍረድ፤ የምትፈርደው በዚች በአነስተኛይቱ ሕይወት ብቻ ነው አሉ፡፡(72) They said, “We will never choose you over the clear signs that have come to us, or over the One Who created us. So decide whatever you will. You can only make a decision about the life of this world.
(73) «ኃጢአቶቻችንንና ከድግምትም በእርሱ ላይ ያስገደድከንን ለእኛ ይምረን ዘንድ እኛ በጌታችን አምነናል፡፡ አላህም በጣም በላጭ ነው፤ (ቅጣቱም) በጣም የሚዘወትር ነው» አሉ፡፡(73) We surely believe in our Lord so that He may forgive us our sins and the magic that you have compelled us to practice, for Allah is best [in reward] and more lasting [in punishment].”
(74) እነሆ ከሓዲ ኾኖ ወደ ጌታው የሚመጣ ሰው ለእርሱ ገሀነም አለችው፡፡ በውስጧም አይሞትም ሕያውም አይኾን፡፡(74) Whoever comes to his Lord as an evildoer, for him is Hell; he will neither die therein nor live.
(75) በጎ ሥራዎችን በእርግጥ የሠራ ምእመን ኾኖ የመጣውም ሰው እነዚያ ለእነሱ ከፍተኛ ደረጃዎች አሏቸው፡፡(75) But whoever comes to Him as a believer, having done righteous deeds, it is they who will have the highest ranks:
(76) ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው የመኖሪያ ገነቶች በውስጣቸው ዘውታሪዎች ሲኾኑ (አሏቸው)፡፡ ይህም የተጥራራ ሰው ምንዳ ነው፡፡(76) Gardens of Eternity, under which rivers flow, abiding therein forever. Such is the reward of those who purify themselves.
(77) ወደ ሙሳም «ባሮቼን ይዘህ በሌሊት ኺድ፡፡ ለእነሱም በባሕር ውስጥ ደረቅ መንገድን አድርግላቸው፡፡ መገኘትን አትፍራ፡፡ (ከመስጠም) አትጨነቅም፡፡» ስንል በእርግጥ ላክንበት፡፡(77) We inspired Moses, “Travel by night with My slaves, and strike for them a dry path across the sea. Have no fear of being overtaken, nor be afraid [of drowning].”
(78) ፈርዖንም ከሰራዊቱ ጋር ኾኖ ተከተላቸው፡፡ ከባህሩም የሚሸፍን ሸፈናቸው፡፡(78) Then Pharaoh pursued them with his soldiers, but they were completely overwhelmed by the sea.
(79) ፈርዖንም ሕዝቦቹን አሳሳታቸው፡፡ ቅኑንም መንገድ አልመራቸውም፡፡(79) Thus Pharaoh led his people astray, and did not guide them.
(80) የእስራኤል ልጆች ሆይ! ከጠላታችሁ በእርግጥ አዳንናችሁ፡፡ በጡርም ቀኝ ጎን ቀጠሮ አደረግንላችሁ፡፡ በእናንተም ላይ መናንና ድርጭትን አወረድንላችሁ፡፡(80) O Children of Israel, We rescued you from your enemy, and made an appointment with you on the right side of Mount Tūr [in Sinai], and sent down for you manna and quails,
(81) ከሰጠናችሁ ሲሳይ፤ ከመልካሙ ብሉ፡፡ በእርሱም ወሰንን አትለፉ፡፡ ቁጣዬ በእናንተ ላይ ይወርድባችኋልና፡፡ በእርሱም ላይ ቁጣዬ የሚወርድበት ሰው በእርግጥ ይጠፋል፡፡(81) [saying], “Eat from the good things We have provided for you, but do not exceed the limits therein, or My wrath will befall you, for anyone upon whom My wrath befalls is perished.
(82) እኔም ለተጸጸተ፣ ላመነም፣ መልካምንም ለሠራ፣ ከዚያም ለተመራ ሰው በእርግጥ መሓሪ ነኝ፡፡(82) I am indeed Most Forgiving to those who repent and believe, and do righteous deeds, then stay on the right path.”
(83) «ሙሳ ሆይ! ከሕዝቦችህ ምን አስቸኮለህም» (ተባለ)፡፡(83) [Allah asked], “What made you hasten from your people, O Moses?”
(84) «እነሱ እነዚህ፤ በዱካዬ ላይ ያሉ ናቸው፡፡ ጌታዬ ሆይ! ትወድልንም ዘንድ ወደ አንተ ቸኮልኩ» አለ፡፡(84) He said, “They are following my footsteps; I hastened to You, my Lord, to please You.”
(85) (አላህ) «እኛም ከአንተ በኋላ ሰዎችህን በእርግጥ ፈትተን፡፡ ሳምራዊውም አሳሳታቸው» አለው፡፡(85) Allah said, “We have certainly tested your people in your absence, and Sāmiri has led them astray.”
(86) ሙሳም ወደ ሰዎቹ የተቆጣ ያዘነ ኾኖ ተመለሰ፡፡ «ሕዝቦቼ ሆይ! ጌታችሁ መልካም ተስፋን አልቀጠራችሁምን ቀጠሮው በእናንተ ላይ ረዘመባችሁን» ወይስ በእናንተ ላይ ከጌታችሁ ቅጣት ሊወርድባችሁ ፈለጋችሁና ቀጠሮየን አፈረሳችሁን አላቸው፡፡(86) So Moses returned to his people, angry and sorrowful. He said, “O my people, did your Lord not promise you a good promise? Was my absence too long for you, or did you want the wrath from your Lord to befall you, so you broke your promise to me?”
(87) «ቀጠሮህን በፈቃዳችን አልጣስንም፡፡ ግን እኛ ከሕዝቦቹ ጌጥ ሸክሞችን ተጫን (በእሳት ላይ) ጣልናትም፡፡ ሳምራዊውም እንደዚሁ ጣለ» አሉት፡፡(87) They said, “We did not break our promise to you out of our own free will, but we were made to carry loads of the people’s jewelry, so we threw them [into the fire], and so did the Sāmiri throw.”
(88) ለእነሱም አካል የኾነ ጥጃን ለእርሱ መጓጎር ያለውን አወጣላቸው፡፡ (ተከታዮቹ) «ይህ አምላካችሁ የሙሳም አምላክ ነው ግን ረሳው» አሉም፡፡(88) Then he moulded for them an image of a calf that made a mooing sound. They said, “This is your god and Moses’ god, but he has forgotten.”
(89) ወደእነሱ ንግግርን የማይመልስ ለእነሱም ጉዳትንና ጥቅምን የማይችል መኾኑን አያዩምን(89) Do they not see that it does not respond a word to them, nor does it have power to harm or benefit them?
(90) ሃሩንም ከዚህ በፊት በእርግጥ አላቸው፡- «ሕዝቦቼ ሆይ! (ይህ) በእርሱ የተሞከራችሁበት ብቻ ነው፡፡ ጌታችሁም አልረሕማን ነው፡፡ ተከተሉኝም፡፡ ትዕዛዜንም ስሙ፡፡»(90) Aaron told them beforehand, “O my people, you are being tested with it. Your Lord is the Most Compassionate, so follow me and obey my command.”
(91) «ሙሳ ወደእኛ እስከሚመለስ በእርሱ (መገዛት) ላይ ከመቆየት ፈጽሞ አንወገድም» አሉ፡፡(91) They said, “We will never cease to worship it until Moses comes back to us.”
(92) (ሙሳ) አለ፡- «ሃሩን ሆይ! ተሳስተው ባየሃቸው ጊዜ ምን ከለከልህ(92) Moses said, “O Aaron, what prevented you when you saw them going astray,
(93) «እኔን ከመከተል ትዕዛዜን ጣስክን»(93) from following me? Did you disobey my command?”
(94) «የእናቴ ልጅ ሆይ! ጢሜንም ራሴንም አትያዝ፡፡ እኔ በእስራኤል ልጆች መካከል ለያየህ፤ ቃሌንም አልጠበቅህም ማለትህን ፈራሁ» አለው፡፡(94) Aaron said, “O son of my mother, do not seize me by my beard or by my head! I feared that you would say, ‘You have caused division among the Children of Israel, and did not heed my words.’”
(95) (ሙሳ) «ሳምራዊው ሆይ! ነገርህም ምንድን ነው» አለ፡፡(95) Moses said, “What is the matter with you, O Sāmiri?”
(96) ያላዩትን ነገር አየሁ፡፡ ከመልክተኛው (ከፈረሱ ኮቴ) ዱካም ጭብጥ አፈርን ዘገንኩ፡፡ (በቅርጹ ላይ) ጣልኳትም፡፡ እንደዚሁም ነፍሴ ሸለመችልኝ» አለ፡፡(96) He said, “I saw something they did not see, so I took a handful [of dust] from the hoof-print of the horse of the messenger [Gabriel] and cast it [into the fire]. This is what my mind prompted me.”
(97) አለው «ኺድ፤ ላንተም በሕይወትህ (ለአየኸው ሰው ሁሉ) መነካካት የለም ማለት አለህ፡፡ ለአንተም ፈጽሞ የማትጣሰው ቀጠሮ አለህ፡፡ ወደዚያም በእርሱ ላይ ተገዢው ኾነህ ወደ ቆየህበት አምላክህ ተመልከት፡፡ በእርግጥ እናቃጥለዋለን፡፡ ከዚያም በባሕሩ ውስጥ መበተንን እንበትነዋለን፡፡»(97) Moses said, “Begone then! Your [punishment] in this life will be to say, ‘Do not touch me,’ but there awaits you an appointed time for your reckoning that you cannot escape. Now look at your so-called god which you kept worshiping; We will surely burn it then scatter it in the sea.
(98) ጌታችሁ ያ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ የኾነው አላህ ብቻ ነው፡፡ እውቀቱ ነገርን ሁሉ አዳረሰ፡፡(98) [O people], your god is only Allah; none has the right to be worshiped except Him. He encompasses everything in knowledge.”
(99) እንደዚሁ በእርግጥ ካለፉት ወሬዎች ባንተ ላይ እንተርካለን፡፡ ከእኛም ዘንድ ቁረኣንን በእርግጥ ሰጠንህ፡፡(99) This is how We relate to you [O Prophet] from the stories of the past, and We have given you a Reminder from Us.
(100) ከእርሱ ያፈገፈገ ሰው እርሱ በትንሣኤ ቀን ከባድን ቅጣት ይሸከማል፡፡(100) Whoever turns away from it will bear a heavy burden on the Day of Resurrection,
(101) በእርሱ ውስጥ ዘውታሪዎች ኾነው (ይሸከማሉ)፡፡ በትንሣኤም ቀን ለእነሱ የኾነው ሸክም ከፋ!(101) abiding therein forever. What a terrible burden they will carry on the Day of Resurrection!
(102) በቀንዱ በሚነፋ ቀን (ሸክማቸው ከፋ)፤ ከሓዲዎችንም በዚያ ቀን (ዓይኖቻቸው) ሰማያዊዎች ሆነው እንሰበስባቸዋለን፡፡(102) the Day when the Trumpet will be blown; on that Day We will gather together the wicked sightless [from horror].
(103) «ዐሥርን (ቀን) እንጂ አልቆያችሁም» በመባባል በመካከላቸው ይንሾካሾካሉ፡፡(103) They will whisper with one another, “You stayed no more than ten days [on earth].”
(104) በሐሳብ ቀጥተኛው «አንድን ቀን እንጅ አልቆያችሁም» በሚል ጊዜ የሚሉትን ነገር እኛ ዐዋቂዎች ነን፡፡(104) We know best what they will say – the most discerning among them will say, “You stayed no more than a day.”
(105) ከጋራዎችም ይጠይቁሃል፤ በላቸው «ጌታዬ መበተንን ይበትናቸዋል፡፡(105) They ask you about the mountains, say, “My Lord will scatter them into dust,
(106) «ትክክል ሜዳም ኾና ይተዋታል፡፡(106) and He will leave the earth level and plain,
(107) «በርሷ ዝቅታና ከፍታን አታይም፡፡»(107) you will not see therein any troughs or peaks.”
(108) በዚያ ቀን (ለመሰብሰብ) ጠሪውን ለእርሱ መጣመም የሌለውን መከተል ይከተላሉ፡፡ ድምጾችም ለአልረሕማን ጸጥ ይላሉ፡፡ ስለዚህ ሹክሹክታን እንጂ አትሰማም፡፡(108) On that day, they will follow the summoner; none will dare to deviate. All voices will be hushed in awe before the Most Compassionate; you will hear nothing except a whisper.
(109) በዚያ ቀን ለእርሱ አልረሕማን የፈቀደለትንና ለእርሱም ቃልን የወደደለትን ሰው ቢኾን እንጅ ምልጃ (አንድንም) አትጠቅምም፡፡(109) On that day, no intercession will be of any use except to whom the Most Compassionate gave permission and approved his word.
(110) በስተፊታቸው ያለውን በስተኋላቸውም ያለውን ሁሉ ያውቃል፡፡ በእርሱም ዕውቀትን አያካብቡም፤ (አያውቁም)፡፡(110) He knows all that is ahead of them and all that is behind them, but they do not encompass it with their knowledge.
(111) ፊቶችም ሁሉ ሕያው አስተናባሪ ለኾነው (አላህ) ተዋረዱ፡፡ በደልንም የተሸከመ ሰው በእርግጥ ከሰረ፡፡(111) All faces will be humbled before the Ever-Living, Self-Sustaining. Those burdened with evil deeds will be in total loss.
(112) እርሱ አማኝ ኾኖ ከመልካም ሥራዎችም የሠራ ሰው በደልንም መጉደልንም አይፈራም፡፡(112) But whoever does righteous deeds, being a believer, will have no fear of being wronged or deprived.
(113) እንደዚሁም ዐረብኛ ቁርኣን ኾኖ አወረድነው፡፡ አላህንም ይፈሩ ዘንድ ወይም ለእነሱ ግሣጼን ያድስላቸው ዘንድ ከዛቻ ደጋግመን በውስጡ ገለጽን፡፡(113) We have sent it down as an Arabic Qur’an and diversified its warnings, so that they may fear Allah or it may cause them to take heed.
(114) እውነተኛው ንጉስ አላህም (ከሓዲዎች ከሚሉት) ላቀ፡፡ ወደ አንተ መወረዱም ከመፈጸሙ በፊት በማንበብ አትቸኩል፡፡ «ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትንም ጨምርልኝ» በል፡፡(114) So Exalted is Allah, the True Sovereign. Do not hasten to [recite] the Qur’an before its revelation to you is concluded, and say, “My Lord, increase me in knowledge.”
(115) ወደ አደምም ከዚህ በፊት ኪዳንን በእርግጥ አወረድን፡፡ ረሳም፡፡ ለእርሱም ቆራጥነትን አላገኘንለትም፡፡(115) We had already given a command to Adam before, but he forgot, and We found him lacking a firm resolve.
(116) ለመላእክትም ለአዳም ስገዱ ባልን ጊዜ (አስታውስ)፡፡ ሰገዱም፤ ኢብሊስ ብቻ ሲቀር እምቢ አለ፡፡(116) When We said to the angels, “Prostrate before Adam,” so they all prostrated, except Iblīs, who refused.
(117) አልንም «አደም ሆይ! ይህ ላንተም ለሚስትህም በእርግጥ ጠላት ነው፡፡ ስለዚህ ከገነት አያውጣችሁ፤ ትለፋለህና፡፡(117) We said “O Adam, this is an enemy to you and to your wife, so do not let him drive you both out of Paradise, for then you will fall into misery.
(118) ለአንተ በእርሷ ውስጥ አለመራብና አለመታረዝ አለህ፡፡(118) Here you will neither go hungry nor naked,
(119) አንተም በርሷ ውስጥ አትጠማም፤ ፀሐይም አትተኮስም፡፡(119) nor will you suffer from thirst or from scorching heat.”
(120) ሰይጣንም ወደርሱ ጎተጎተ «አደም ሆይ! በመዘውተሪያ ዛፍ በማይጠፋ ንግሥናም ላይ ላመላክትህን አለው፡፡(120) Then Satan whispered to him, and said, “O Adam, shall I show you the tree of immortality and a kingdom that will never decay?”
(121) ከእርሷም በልሉ፡፡ ለእነርሱም ኀፍረተ ገላቸው ተገለጸች፡፡ ከገነትም ቅጠል በላያቸው ላይ ይለጥፉ ጀመር፡፡ አደምም የጌታውን ትእዛዝ (ረስቶ) ጣሰ፡፡ (ከፈለገው መዘውተር) ተሳሳተም፡፡(121) So they both ate from the tree, then their nakedness was revealed to each other, and they began to put together leaves from Paradise to cover themselves. Thus Adam disobeyed his Lord, and fell into error.
(122) ከዚያም ጌታው መረጠው ከእርሱም ጸጸቱን ተቀበለው መራውም፡፡(122) Thereafter his Lord chose him, accepted his repentance, and guided him.
(123) አላቸው «ከፊላችሁም ለከፊሉ ጠላት ሲኾን ሁላችሁም ከእርሷ ውረዱ ከእኔም የኾነ መሪ ቢመጣላችሁ መሪየን የተከተለ አይሳሳትም አይቸገርምም፡፡(123) Allah said, “Get down, both of you, from here altogether [with Satan] as enemies to one another. Then when there comes to you guidance from Me, whoever follows My guidance will neither go astray nor fall into misery.
(124) «ከግሣጼዬም የዞረ ሰው ለእርሱ ጠባብ ኑሮ አለው፡፡ በትንሣኤም ቀን ዕውር ኾኖ እንቀሰቅሰዋለን፡፡(124) But whoever turns away from My Reminder will have a miserable life, and on the Day of Resurrection We will raise him blind.”
(125) «ጌታዬ ሆይ! ለምን ዕውር አድርገህ አስነሳኸኝ በእርግጥ የማይ የነበርኩ ስኾን» ይላል፡፡(125) He will say, “My Lord, why have you raised me blind, when I was able to see before?”
(126) (ነገሩ) እንደዚሁ ነው፡፡ «ታምራታችን መጣችልህ፡፡ ተውካትም፡፡ እንደዚሁም ዛሬ ትተዋለህ» ይለዋል፡፡(126) Allah will say, “Similarly Our verses came to you, but you ignored them, so you will be ignored Today.”
(127) እንደዚሁም ያጋራንና በጌታው አንቀጾች ያላመነን ሰው እንቀጣዋለን፡፡ የመጨረሻይቱም ዓለም ቅጣት በጣም ብርቱ ሁልጊዜ ዘውታሪም ነው፡፡(127) This is how We recompense those who transgress the limits and do not believe in the verses of his Lord; and the punishment of the Hereafter is more severe and more lasting.
(128) (ቁረይሾች) ከእነሱ በፊት ከክፍለ ዘመናት ሕዝቦች ብዙዎችን ያጠፋን መኾናችን በመኖሪያዎቻቸው የሚኼዱ ኾነው ሳሉ ለእነርሱ አልተገለጸላቸውምን በዚህ ውስጥ ለአእምሮ ባለቤቶች በእርግጥ መልክቶች አሉበት፡፡(128) Is it not yet clear to them how many generations We destroyed before them, in whose dwellings they still walk about? There are signs in this for people of sound intellect.
(129) ከጌታህ ያለፈች ቃልና የተወሰነ ጊዜ ባልነበረ ኖሮ (ቅጣቱ አሁኑኑ) የሚይዛቸው ይኾን ነበር፡፡(129) Were it not for a prior decree from your Lord [O Prophet] and a time already set, they would have already been punished.
(130) በሚሉትም ላይ ታገስ፡፡ ጌታህንም ፀሐይ ከመውጣትዋ በፊት ከመግባትዋም በፊት የምታመሰግን ኾነህ አጥራው፤ (ስገድ)፡፡ ከሌሊት ሰዓቶችም በቀን ጫፎችም አጥራው፡፡ (በሚሰጥህ ምንዳ) ልትወድ ይከጀላልና፡፡(130) So be patient with what they say, and glorify your Lord with praise before sunrise and before sunset, and glorify Him during the night and at both ends of the day, so that you may be pleased [with the reward].
(131) ዓይኖችህንም ከእነርሱ (ከሰዎቹ) ክፍሎችን በእርሱ ልንፈትናቸው ወደ አጣቀምንበት፤ ወደ ቅርቢቱ ሕይወት ጌጦች አትዘርጋ፡፡ የጌታህ ሲሳይም በጣም በላጭ ዘውታሪም ነው፡፡(131) Do not turn your eyes covetously towards the various forms of splendor of this life that We have given some of the [disbelievers] to enjoy, as a trial for them. But the provision of your Lord is far better and more lasting.
(132) ቤተሰብህንም በስግደት እዘዝ፡፡ በእርሷም ላይ ዘውትር፤(ጽና)፡፡ ሲሳይን አንጠይቅህም፡፡ እኛ እንሰጥሃለን፡፡ መልካሚቱ መጨረሻም ለጥንቁቆቹ ናት፡፡(132) Enjoin your household to perform prayer and adhere to it firmly. We ask no provision from you; rather, it is We Who give you provision. And the best outcome is for those who fear Allah.
(133) «ከጌታውም በኾነ ተዓምር አይመጣንምን» አሉ በመጀመሪያዎቹ ጽሑፎች ውስጥ ያለችው ማስረጃ አልመጣቻቸውምን(133) They say, “Why does he not bring us a sign from his Lord?” Has there not come to them [the Qur’an as] a confirmation of what is in the earlier Scriptures?
(134) እኛም ከእርሱ (ከሙሐመድ መላክ) በፊት በቅጣት ባጠፋናቸው ኖሮ «ጌታችን ሆይ! ከመዋረዳችንና ከማፈራችን በፊት አንቀጾችህን እንከተል ዘንድ ወደኛ መልከተኛን አትልክም ነበርን» ባሉ ነበር፡፡(134) If We had destroyed them with a punishment before this, they would have said, “Our Lord, if only You had sent us a messenger so that we would have followed Your verses before being humiliated and disgraced.”
(135) «ሁሉም ተጠባባቂ ነው፡፡ ተጠባበቁም፡፡ የቀጥታውም መንገድ ባለቤቶች እነማን እንደሆኑ እነማንም እንደ ተመሩ ወደ ፊት ታውቃላችሁ» በላቸው፡፡(135) Say, “Each of us is waiting, so wait! You will come to know who are the people of the straight path and who are rightly guided.”

One thought on “20 – Taa-Haa 

  1. ተመዝግቤ ግን በነፃ ማንበብ ፈልጌ ነበር እንደት ነው የማገኘው ይሃን ሱራ?

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

41 – Fussilat

41 – Fussilat (1) ሐ.መ.(ሓ ሚም)፡፡ (1) Hā Mīm. (2) (ይህ ቁርኣን) እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ ከሆነው (አላህ) የተወረደ ነው፡፡ (2) A revelation…

87 – Al-A’laa

87 – Al-A’laa (1) ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡ (1) Glorify the name of your Lord, the Most High,…

78 – An-Naba

78 – An-Naba (1) ከምን ነገር ይጠያየቃሉ? (1) About what are they asking one another? (2) ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡ (2)…