Skip to content

Amharic Quran

ከመሞትህ በፊት ቁርአንን አንብብ! (Read the holy Quran before you die!)

  • Home
    • ቁርአንን እንረዳው
    • Download
  • ሱራዎች / Surah List
    • አል-ፋቲሐ (Al-Fatiha)
    • አል-በቀራህ (Al-Beqerah)
    • አል-ዒምራን (Al-Imran)
    • አል-ኒሳዕ (An-Nisa)
    • አል-ማዒዳህ (Al-Maidah) 
    • አንዓም (Al-anam)
    • አል አዕራፍ (Al-Aeraf)
    • አል አንፋል (Al-Anfal)
    • አል ተውባ (At-Tawba)
    • አል ዩኑስ (Yunus)
    • አል ሁድ (Al-Hud)
    • ዩሱፍ (Yusuf)
    • 13 – Ar-Ra’d
    • 14 – Ibrahim
    • አል ሒጅር (Al-Hijr)
    • 16 – An-Nahl
    • 17 – Al-Israa
    • ከህፍ (Al-Kahf )
    • 19 Maryam
    • ጧሃ (Taa-Ha)
    • 21 – Al-Anbiyaa
    • አል ሐጅ (Al-Hajj)
    • 23 – Al-Muminoon
    • 24 – An-Noor
    • 25 – Al -Furqan
    • 26 – Ash-Shu’araa
    • 27 – An-Naml
    • 28 – Al-Qasas
    • 29 – Al-Ankaboot
    • 30 – Ar-Room
    • 31 – Luqman
    • 32 – As-Sajda
    • 33 – Al-Ahzaab
    • 34 – Saba
    • 35 – Faatir
    • 36 – Yaseen
    • 37 – As-Saaffaat
    • 38 – Saad
    • 39 – Az-Zumar
    • 40 – Al-Ghaafir
    • 41 – Fussilat
    • 42 – Ash-Shura
    • 43 – Az-Zukhruf
    • 44 – Ad-Dukhaan
    • 45 – Al-Jaathiya
    • 46 – Al-Ahqaf
    • 47 – Muhammad
    • 48 – Al-Fath
    • 49 – Al-Hujuraat
    • 50 – Qaaf
    • 51 – Adh-Dhaariyat
    • 52 – At-Tur
    • 53 – An-Najm
    • 54 – Al-Qamar
    • 55 – Ar-Rahmaan
    • 56 – Al-Waaqia
    • 57 – Al-Hadid
    • 58 – Al-Mujaadila
    • 59 – Al-Hashr
    • 60 – Al-Mumtahana
    • 61 – As-Saff
    • 62 – Al-Jumu’a
    • 63 – Al-Munaafiqoon
    • 64 – At-Taghaabun
    • 65 – At-Talaaq
    • 66 – At-Tahrim
    • 67 – Al-Mulk
    • 68 – Al-Qalam
    • 69 – Al-Haaqqa
    • 70 – Al-Ma’aarij
    • 71 – Nooh
    • 72 – Al-Jinn
    • 73 – Al-Muzzammil
    • 74 – Al-Muddaththir
    • 75 – Al-Qiyaama
    • 76 – Al-Insaan
    • 77 – Al-Mursalaat
    • 78 – An-Naba
    • 79 – An-Naazi’aat
    • 80 – Abasa
    • 81 – At-Takwir
    • 82 – Al-Infitaar
    • 83 – Al-Mutaffifin
    • 84 – Al-Inshiqaaq
    • 85 – Al-Burooj
    • 86 – At-Taariq
    • 87 – Al-A’laa
    • 88 – Al-Ghaashiya
    • 89 – Al-Fajr
    • 90 – Al-Balad
    • 91 – Ash-Shams
    • 92 – Al-Lail
    • 93 – Ad-Dhuhaa
    • 94 – Ash-Sharh
    • 95 – At-Tin
    • 96 – Al-Alaq
    • 97 – Al-Qadr
    • 98 – Al-Bayyina
    • 99 – Az-Zalzala
    • 100 – Al-Aadiyaat
    • 101 – Al-Qaari’a
    • 102 – At-Takaathur
    • 103 – Al-Asr
    • 104 – Al-Humaza
    • 105 – Al-Fil
    • 106 – Quraish
    • 107 – Al-Maa’un
    • 108 – Al-Kawthar
    • 109 – Al-Kaafiroon
    • 110 – An-Nasr
    • 111 – Al-Masad
    • 112 – Al-Ikhlaas
    • 113 – Al-Falaq
    • 114 – An-Naas

20 – Taa-Haa Amharic Quran ሱረቱ ጧሃ

Posted on November 21, 2023August 5, 2026 By Muhammed No Comments on 20 – Taa-Haa Amharic Quran ሱረቱ ጧሃ
Amharic Quran, ቁርአንን እንረዳው
بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَـٰنِ الرَّحِيمِ
(١) طه
1. ጧሃ፤
(1) Tā Ha
(٢) مَا أَنزَلْنَا عَلَيْكَ الْقُرْآنَ لِتَشْقَىٰ
2.(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ቁርኣንን አንድትቸገር ባንተ ላይ አላወረድንም።
(2) We have not sent down the Qur’an to you [O Prophet] to cause you distress,
(٣) إِلَّا تَذْكِرَةً لِّمَن يَخْشَىٰ
3. አላህን ለሚፈራ ሁሉ መገሠጫ ይሆን ዘንድ እንጂ
(3) but as a reminder for those who fear Allah.
(٤) تَنزِيلًا مِّمَّنْ خَلَقَ الْأَرْضَ وَالسَّمَاوَاتِ الْعُلَى
4. ቁርኣን ምድርንና የላይኛዎቹን (የተከበሩ) ሰማያትን ከፈጠረ አምላክ ተወረደ።
(4) A revelation from the One Who created the earth and the high heavens.
(٥) الرَّحْمَـٰنُ عَلَى الْعَرْشِ اسْتَوَىٰ
5.እርሱ አዛኙ ጌታ (አር-ረህማን) በዐርሹ ላይ ከፍ አለ።
(5) The Most Compassionate rose over the Throne.
(٦) لَهُ مَا فِي السَّمَاوَاتِ وَمَا فِي الْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا وَمَا تَحْتَ الثَّرَىٰ
6. በሰማያት፤በምድርና በመካከላቸዉም ያለው ከአፈር በታችም ያለው ሁሉ የእርሱ ብቻ ነው።
(6) To Him belongs all that is in the heavens and all that is on earth, and all that is between them, and all that is beneath the soil.
(٧) وَإِن تَجْهَرْ بِالْقَوْلِ فَإِنَّهُ يَعْلَمُ السِّرَّ وَأَخْفَى
7. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በንግግር ብትጮህ (አላህ ከጩኸቱ የተብቃቃ ነው።) እርሱ ምስጢርን ከዚያም በጣም የተደበቀንም ያውቃልና።
(7) Whether you speak loudly [or not], He surely knows what is secret and what is even more hidden.
(٨) اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ لَهُ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ
8.አላህ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም። ለእርሱ መልካሞች የሆኑ አያሌ ስሞች አሉት።
(8) Allah – none has the right to be worshiped except Him. He has the Most Beautiful Names.
(٩) وَهَلْ أَتَاكَ حَدِيثُ مُوسَىٰ
9.(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሙሳ ወሬ (ታሪክ) መጥቶሃልን (ደርሶሃልን)?
(9) Has there come to you the story of Moses?
(١٠) إِذْ رَأَىٰ نَارًا فَقَالَ لِأَهْلِهِ امْكُثُوا إِنِّي آنَسْتُ نَارًا لَّعَلِّي آتِيكُم مِّنْهَا بِقَبَسٍ أَوْ أَجِدُ عَلَى النَّارِ هُدًى
10. እሳትን ባየና ለቤተሰቦቹ «(እዚህ) ቆዩ። እኔ እሳትን አየሁ፤ ከእርሷ ችቦን ላመጣላችሁ ወይም እሳቲቱ ዘንድ መሪን ላገኝ እከጅላለሁ።» ባለ ጊዜ የሆነውን አስታውስ።
(10) When he saw a fire, he said to his family, “Stay here. I have spotted a fire; I may bring you a flaming brand from it, or find some guidance at the fire.”
(١١) فَلَمَّا أَتَاهَا نُودِيَ يَا مُوسَىٰ
11. እናም ወደ እርሷ በመጣ ጊዜ (እንዲህ) በማለት ተጠራ: «ሙሳ ሆይ!
(11) When he came to it, he was called, “O Moses,
(١٢) إِنِّي أَنَا رَبُّكَ فَاخْلَعْ نَعْلَيْكَ ۖ إِنَّكَ بِالْوَادِ الْمُقَدَّسِ طُوًى
12. «እኔ ጌታህ ነኝ። ጫማዎችህን አውልቅ፤ አንተ በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ ነህና።
(12) Indeed, I am your Lord, so take off your shoes; you are in the sacred valley of Tuwā.
(١٣) وَأَنَا اخْتَرْتُكَ فَاسْتَمِعْ لِمَا يُوحَىٰ
13. «እኔም መረጥኩህ ስለ ሆነም የሚወረድልህን ነገር በደንብ አዳምጥ።
(13) I have chosen you, so listen to what is being revealed:
(١٤) إِنَّنِي أَنَا اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدْنِي وَأَقِمِ الصَّلَاةَ لِذِكْرِي
14. «እኔ አላህ ነኝ። ያለ እኔ ትክክለኛ አምላክ የለምና እኔን ብቻ ተገዛኝ። ሶላትንም እኔን ለማውሳት በአግባቡ ስገድ።
(14) ‘Indeed, I am Allah; none has the right to be worshiped except Me, so worship Me and establish prayer to remember me.
(١٥) إِنَّ السَّاعَةَ آتِيَةٌ أَكَادُ أُخْفِيهَا لِتُجْزَىٰ كُلُّ نَفْسٍ بِمَا تَسْعَىٰ
15. «ነፍስ ሁሉ በምትሰራው ነገር ትመነዳ ዘንድ ሰዓቲቱ በእርግጥ መጪ ናት። የትንሳኤውን ወሬ ልደብቃት እቀርባለሁ።
(15) The Hour is certainly coming, but I almost keep it hidden, so that every soul will be recompensed for what it strives.
(١٦) فَلَا يَصُدَّنَّكَ عَنْهَا مَن لَّا يُؤْمِنُ بِهَا وَاتَّبَعَ هَوَاهُ فَتَرْدَىٰ
16. (ሙሳ ሆይ!) «በእርሷ የማያምንና ዝንባሌውን የሚከተል ሰው ሁሉ ከእርሷ አያግድህ ትጠፋለህና።
(16) So do not let those who disbelieve in it and follow their desires distract you from it, or you will perish.’”
(١٧) وَمَا تِلْكَ بِيَمِينِكَ يَا مُوسَىٰ
17. (ሙሳ ሆይ!) «ይህችም በቀኝ እጅህ ያለችው ምንድን ናት?» (ተባለ)።
(17) What is that in your right hand, O Moses?”
(١٨) قَالَ هِيَ عَصَايَ أَتَوَكَّأُ عَلَيْهَا وَأَهُشُّ بِهَا عَلَىٰ غَنَمِي وَلِيَ فِيهَا مَآرِبُ أُخْرَىٰ
18. «እርሷ በትሬ ናት። በእርሷም እደገፍባታለሁ። በእርሷም ለፍየሎቼ ቅጠልን አረግፍባታለሁ። በእርሷ ሌሎች ጉዳዮችም አሉኝ።» አለ።
(18) He said, “It is my staff. I lean on it and beat down leaves with it for my sheep, and I have other uses for it.”
(١٩) قَالَ أَلْقِهَا يَا مُوسَىٰ
19. አላህም «ሙሳ ሆይ! እስቲ ጣላት።» አለው።
(19) Allah said, “Throw it down, O Moses!”
(٢٠) فَأَلْقَاهَا فَإِذَا هِيَ حَيَّةٌ تَسْعَىٰ
20.ሙሳም ጣላትና፤ ወዲያዉም እርሷ የምትሮጥ እባብ ሆነች።
(20) He threw it down, and it suddenly became a slithering snake.
(٢١) قَالَ خُذْهَا وَلَا تَخَفْ ۖ سَنُعِيدُهَا سِيرَتَهَا الْأُولَىٰ
21.አላህም አለው: «ሙሳ ሆይ! ያዛት አትፍራም ወደ መጀመሪያ ጠባይዋ እንመልሳታለን።
(21) Allah said, “Pick it up, and have no fear. We will restore it to its former state.
(٢٢) وَاضْمُمْ يَدَكَ إِلَىٰ جَنَاحِكَ تَخْرُجْ بَيْضَاءَ مِنْ غَيْرِ سُوءٍ آيَةً أُخْرَىٰ
22. «እጅህንም ወደ ብብትህ አስገባ። ሌላ ተዓምር ስትሆን ያለ ምንም ችግር ነጭ ሆና ትወጣለችና።
(22) Put your hand under your armpit; it will come out shining white without blemish, as another sign,
(٢٣) لِنُرِيَكَ مِنْ آيَاتِنَا الْكُبْرَى
23. (ሙሳ ሆይ!) «ከተዓምራቶቻችን ታላቋን እናሳይህ ዘንድ ይህን ፈጸምን።
(23) so that We may show you some of Our greatest signs.
(٢٤) اذْهَبْ إِلَىٰ فِرْعَوْنَ إِنَّهُ طَغَىٰ
24. (ሙሳ ሆይ!) «ወደ ፈርዖን ሂድ። እርሱ ወሰን (ድንበር) አልፏልና።»
(24) Go to Pharaoh, for he has transgressed all bounds.”
(٢٥) قَالَ رَبِّ اشْرَحْ لِي صَدْرِي
25. ሙሳም አለ: «ጌታዬ ሆይ! ልቤን አስፋልኝ።
(25) He said, “My Lord, reassure my heart for me,
(٢٦) وَيَسِّرْ لِي أَمْرِي
26. «ጉዳዬንም አግራልኝ።
(26) and ease my task for me,
 
(٢٧) وَاحْلُلْ عُقْدَةً مِّن لِّسَانِي
27. «የምላሴን መኮላተፍም አስወግድልኝ።
(27) and loosen the knot from my tongue,
(٢٨) يَفْقَهُوا قَوْلِي
28. «ንግግሬን ይረዱ ዘንድ።
(28) so that they may understand my speech.
(٢٩) وَاجْعَل لِّي وَزِيرًا مِّنْ أَهْلِي
29. «ከቤተሰቦቼም ለእኔ ረዳትን አድርግልኝ።
(29) And appoint for me a helper from my family,
(٣٠) هَارُونَ أَخِي
30. «ወንድሜን ሃሩንን
(30) Aaron, my brother.
 
(٣١) اشْدُدْ بِهِ أَزْرِي
31. «ኃይሌንም በእርሱ አበርታልኝ።
(31) Increase my strength through him,
(٣٢) وَأَشْرِكْهُ فِي أَمْرِي
32. «በነገሬም አጋራው።
(32) and let him share my task,
 
(٣٣) كَيْ نُسَبِّحَكَ كَثِيرًا
33. «በብዛት እንድናጠራህና
(33) so that we may glorify You much,
(٣٤) وَنَذْكُرَكَ كَثِيرًا
34. «በብዛት እንድናወሳህ
(34) and remember You much.
 
(٣٥) إِنَّكَ كُنتَ بِنَا بَصِيرًا
35. «አንተ በእኛ ነገር አዋቂ ነህና።»
(35) For indeed You are All-Watchful over us.”
(٣٦) قَالَ قَدْ أُوتِيتَ سُؤْلَكَ يَا مُوسَىٰ
36. አላህም አለ: «ሙሳ ሆይ! ልመናህ በእርግጥ ተቀባይነትን አገኝቷል።
(36) Allah said, “You are granted your request, O Moses.
(٣٧) وَلَقَدْ مَنَنَّا عَلَيْكَ مَرَّةً أُخْرَىٰ
37. «ሙሳ ሆይ! በሌላም ጊዜ ባንተ ላይ በእርግጥ ውለታን ውለናል።
(37) And We had already conferred favor upon you before,
(٣٨) إِذْ أَوْحَيْنَا إِلَىٰ أُمِّكَ مَا يُوحَىٰ
38. «ለእናትህ በራእይ ባሳወቅን ጊዜ ነው።
(38) when We inspired your mother, saying,
(٣٩) أَنِ اقْذِفِيهِ فِي التَّابُوتِ فَاقْذِفِيهِ فِي الْيَمِّ فَلْيُلْقِهِ الْيَمُّ بِالسَّاحِلِ يَأْخُذْهُ عَدُوٌّ لِّي وَعَدُوٌّ لَّهُ ۚ وَأَلْقَيْتُ عَلَيْكَ مَحَبَّةً مِّنِّي وَلِتُصْنَعَ عَلَىٰ عَيْنِي
39. «‹ሕፃኑን በሳጥኑ ውስጥ አስገቢው እርሱንም (ሳጥኑን) በባህር ላይ ጣይው፤ ባህሩም በዳርቻው ይጥለዋል (ይተፋዋል)። ለእኔም ለእርሱም ጠላት የሆነ ሰው ይይዘዋልና› በማለት (ባሳወቅን ጊዜ ለገስንልህ)። ልትወደድና በዐይኔ እይታ (በእኔም ጥበቃ) ታድግ ዘንድ ባንተ ላይም ከእኔ የሆነ መወደድን ጣልኩብህ።
(39) ‘Put him into the casket, then cast it into the river. The river will carry it to the shore, and he will be picked up by one who is an enemy to Me and enemy to him.’ I bestowed upon you love from Myself so that you would be brought up under My [watchful] Eye.
(٤٠) إِذْ تَمْشِي أُخْتُكَ فَتَقُولُ هَلْ أَدُلُّكُمْ عَلَىٰ مَن يَكْفُلُهُ ۖ فَرَجَعْنَاكَ إِلَىٰ أُمِّكَ كَيْ تَقَرَّ عَيْنُهَا وَلَا تَحْزَنَ ۚ وَقَتَلْتَ نَفْسًا فَنَجَّيْنَاكَ مِنَ الْغَمِّ وَفَتَنَّاكَ فُتُونًا ۚ فَلَبِثْتَ سِنِينَ فِي أَهْلِ مَدْيَنَ ثُمَّ جِئْتَ عَلَىٰ قَدَرٍ يَا مُوسَىٰ
40. «እህትህ በምትሄድና ‹የሚያሳድገውን ሰው ላመላክታችሁን?› ባለች ጊዜ (መወደድን ጣልኩብህ)። ወደ እናትህም ዓይኗ እንዲረጋና እርሷ እንዳታዝንም መለስንህ። ነፍስንም ገደልክ ከጭንቅም አዳንንህ። ፈተናዎችንም ፈተንህ። በመድየን ቤተሰቦችም ውስጥ ብዙ ዓመታትን ተቀመጥክ። ከዚያ ሙሳ ሆይ! በተወሰነ ጊዜ ላይ መጣህ።
(40) When your sister was going along and said, ‘Shall I show you someone who will nurse him?’ Thus We brought you back to your mother, so that she may rejoice and not grieve. Then you killed a man [by mistake], but We saved you from distress, and We put you through several trials. You stayed among the people of Midian for several years, then you came [here] at a destined time, O Moses.
(٤١) وَاصْطَنَعْتُكَ لِنَفْسِي
41. «ለራሴም ለመልዕክተኝነት መረጥኩህ።
(41) I have chosen you for Myself.
(٤٢) اذْهَبْ أَنتَ وَأَخُوكَ بِآيَاتِي وَلَا تَنِيَا فِي ذِكْرِي
42. «አንተና ወንድምህ በተዓምራቴ ሆናችሁ ሂዱ። እኔንም ከማውሳትም አትቦዝኑ።
(42) Go forth, you and your brother, with My signs and do not slacken in remembering Me.
(٤٣) اذْهَبَا إِلَىٰ فِرْعَوْنَ إِنَّهُ طَغَىٰ
43. «ወደ ፈርዖን ሂዱ። እርሱ ወሰን አልፏልና።
(43) Go, both of you, to Pharaoh, for he has certainly transgressed all bounds.
(٤٤) فَقُولَا لَهُ قَوْلًا لَّيِّنًا لَّعَلَّهُ يَتَذَكَّرُ أَوْ يَخْشَىٰ
44. «እርሱ ምን አልባትም ይገሰጥ ወይም ይፈራ ዘንድ። ለእርሱ ለስላሳን ቃል ተናገሩት።»
(44) But speak to him gently, so that he may take heed or fear Allah.”
(٤٥) قَالَا رَبَّنَا إِنَّنَا نَخَافُ أَن يَفْرُطَ عَلَيْنَا أَوْ أَن يَطْغَىٰ
45. «ጌታችን ሆይ! በእኛ ላይ ክፋት በመስራት መቸኮሉን ወይም ኩራትን መጨመሩን እንፈራለን።» አሉ።
(45) They said, “Our Lord, we fear that he may hasten to punish us or transgress all bounds.”
(٤٦) قَالَ لَا تَخَافَا ۖ إِنَّنِي مَعَكُمَا أَسْمَعُ وَأَرَىٰ
46. አላህም አለ: «እኔ በእርግጥ ከናንተ ጋር ነኝና አትፍሩ። የሚለውንም ሁሉ እሰማለሁ። የሚፈጸመዉንም አያለሁም።
(46) He said, “Do not be afraid; I am with you both, hearing and seeing.
(٤٧) فَأْتِيَاهُ فَقُولَا إِنَّا رَسُولَا رَبِّكَ فَأَرْسِلْ مَعَنَا بَنِي إِسْرَائِيلَ وَلَا تُعَذِّبْهُمْ ۖ قَدْ جِئْنَاكَ بِآيَةٍ مِّن رَّبِّكَ ۖ وَالسَّلَامُ عَلَىٰ مَنِ اتَّبَعَ الْهُدَىٰ
47. እናም ወደ እርሱም ሂዱና (እንዲህ) በሉት: ‹እኛ የጌታህ መልዕክተኞች ነንና የኢስራኢልን ልጆች ሁሉ ከእኛ ጋር ልቀቅ። አታሰቃያቸዉም። ከጌታህ በሆነው ተዓምር በእርግጥ መጥተንሃልና። ሰላምም ቀጥታን በተከተለ ሁሉ ላይ ይሁን።
(47) So go to him and say, ‘We are both messengers from your Lord, so let the Children of Israel go with us and do not oppress them. We have come to you with a sign from your Lord; and peace be upon he who follows the true guidance.
(٤٨) إِنَّا قَدْ أُوحِيَ إِلَيْنَا أَنَّ الْعَذَابَ عَلَىٰ مَن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ
48. «‹እነሆ የአላህ ቅጣት እውነትን ባስተባበለና እምቢ ባለ ሰው ላይ እንደሆነ በእርግጥ አያሌ መልዕክት ተወረደልን።› በሉት።»
(48) It has been revealed to us that the punishment awaits those who reject [the truth] and turn away.’”
(٤٩) قَالَ فَمَن رَّبُّكُمَا يَا مُوسَىٰ
49. ፈርዖንም «ሙሳ ሆይ! ጌታችሁ ማነው?» አለ።
(49) Pharaoh said, “So who is the Lord of you two, O Moses?”
(٥٠) قَالَ رَبُّنَا الَّذِي أَعْطَىٰ كُلَّ شَيْءٍ خَلْقَهُ ثُمَّ هَدَىٰ
50. «ጌታችን ያ ለፍጥረቱ ሁሉ የሚያስፈልገውን ቅርጹንና ባህሪውን የሰጠው ከዚያም ሁሉንም ለተፈጠረለት የመራው ነው።» አለው።
(50) He said, “Our Lord is the One Who gave everything its form then guided it.”
(٥١) قَالَ فَمَا بَالُ الْقُرُونِ الْأُولَىٰ
51. ፈርዖንም «የመጀመሪያይቱ ዘመናት ህዝቦች ሁኔታስ ምንድን ነው?» አለ።
(51) Pharaoh said, “Then what about the former [disbelieving] nations?”
(٥٢) قَالَ عِلْمُهَا عِندَ رَبِّي فِي كِتَابٍ ۖ لَّا يَضِلُّ رَبِّي وَلَا يَنسَى
52. ሙሳም «የዚህ ዕውቀት እጌታዬ ዘንድ በመጽሐፍ የተመዘገበ ነው። ጌታዬ አይሳሳትም አይረሳምም።» አለው።
(52) He said, “Its knowledge is with my Lord in a Record. My Lord never errs, nor does He forget.”
(٥٣) الَّذِي جَعَلَ لَكُمُ الْأَرْضَ مَهْدًا وَسَلَكَ لَكُمْ فِيهَا سُبُلًا وَأَنزَلَ مِنَ السَّمَاءِ مَاءً فَأَخْرَجْنَا بِهِ أَزْوَاجًا مِّن نَّبَاتٍ شَتَّىٰ
53. ያ ምድርን ለእናንተ ምንጣፍ ያደረገላችሁ በእርሷም ውስጥ ለእናንተ መንገድን ያገራላችሁ ውሃንም ከሰማይ ያወረደላችሁ ነው። በእርሱም ከተለያየ በቃይ ዓይነቶችን አወጣንላችሁ።
(53) It is He Who spread out the earth for you and made therein pathways for you, and sent down rain from the sky; and We brought forth thereby various types of plants.
(٥٤) كُلُوا وَارْعَوْا أَنْعَامَكُمْ ۗ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَاتٍ لِّأُولِي النُّهَىٰ
54. ለራሳችሁ ብሉ። እንስሳዎቻችሁንም አግጡ። (ባዮች ሆነን አወጣንላችሁ።) በዚህ ውስጥ ለአእምሮ ባለቤቶች ሁሉ በእርግጥ ተዐምራት አለበት።
(54) Eat and graze your livestock. Indeed, there are signs in this for people of sound intellect.
(٥٥) مِنْهَا خَلَقْنَاكُمْ وَفِيهَا نُعِيدُكُمْ وَمِنْهَا نُخْرِجُكُمْ تَارَةً أُخْرَىٰ
55. (ሰዎች ሆይ!) ከእርሷ (ከምድር) ፈጠርናችሁ። ወደ እርሷም ውስጥ እንመልሳችኋለን። ከእርሷም በሌላ ጊዜ እናወጣችኋለን።
(55) From this [earth] We created you, and to it We will return you, and from it We will raise you once again.
(٥٦) وَلَقَدْ أَرَيْنَاهُ آيَاتِنَا كُلَّهَا فَكَذَّبَ وَأَبَىٰ
56.ተዓምራቶቻችንንም ሁሏንም ለፈርዖን በእርግጥ አሳየነው። አስተባበለም። እምቢም አለ።
(56) We showed Pharaoh all Our signs, but he rejected them and refused to believe.
(٥٧) قَالَ أَجِئْتَنَا لِتُخْرِجَنَا مِنْ أَرْضِنَا بِسِحْرِكَ يَا مُوسَىٰ
57. አለም: «ሙሳ ሆይ! ከምድራችን በድግምትህ ልታወጣን መጣህብን?
(57) He said, “Have you come to drive us out of our land with your magic, O Moses?
(٥٨) فَلَنَأْتِيَنَّكَ بِسِحْرٍ مِّثْلِهِ فَاجْعَلْ بَيْنَنَا وَبَيْنَكَ مَوْعِدًا لَّا نُخْلِفُهُ نَحْنُ وَلَا أَنتَ مَكَانًا سُوًى
58. «መሰሉንም ድግምት እናመጣብሃለን። በእኛና ባንተም መካከል እኛም አንተም የማንጥሰው የሆነ ቀጠሮን በመካከለኛ ስፍራ አድርግልን።» አለ።
(58) We will surely bring you similar magic. So appoint a day between us that neither you nor we will fail to keep, in a convenient place.”
(٥٩) قَالَ مَوْعِدُكُمْ يَوْمُ الزِّينَةِ وَأَن يُحْشَرَ النَّاسُ ضُحًى
59.ሙሳም: «ቀጠሯችሁ ያ የማጌጫው የበአሉ ቀን ነው። ሰዎችም ረፋድ ላይ እንዲሰበሰቡ ይሁን።» አለ።
(59) Moses said, “Your appointment is the festival day; let the people be gathered at forenoon.”
(٦٠) فَتَوَلَّىٰ فِرْعَوْنُ فَجَمَعَ كَيْدَهُ ثُمَّ أَتَىٰ
60. ፈርዖንም ዞረ። ተንኮሉን ሰበሰበ። ከዚያ መጣ።
(60) So Pharaoh went away and put together his scheme, then came forth.
(٦١) قَالَ لَهُم مُّوسَىٰ وَيْلَكُمْ لَا تَفْتَرُوا عَلَى اللَّهِ كَذِبًا فَيُسْحِتَكُم بِعَذَابٍ ۖ وَقَدْ خَابَ مَنِ افْتَرَىٰ
61.ሙሳም ለእነርሱ: «ወዮላችሁ በአላህ ላይ ውሸትን አትቅጠፉ። በቅጣት ያጠፋችኋልና። የቀጠፈም ሰው በእርግጥ አፈረ።» አላቸው።
(61) Moses said to them, “Woe to you, do not fabricate lies against Allah, lest He exterminate you with a punishment. Those who fabricate lies are bound to fail.”
(٦٢) فَتَنَازَعُوا أَمْرَهُم بَيْنَهُمْ وَأَسَرُّوا النَّجْوَىٰ
62. (ድግምተኞቹ) በመካከላቸውም ነገራቸውን ተጨቃጨቁ፡፡ ውይይትንም ደበቁ፡፡
(62) Then they disputed the matter among themselves, and kept their talk private.
(٦٣) قَالُوا إِنْ هَـٰذَانِ لَسَاحِرَانِ يُرِيدَانِ أَن يُخْرِجَاكُم مِّنْ أَرْضِكُم بِسِحْرِهِمَا وَيَذْهَبَا بِطَرِيقَتِكُمُ الْمُثْلَىٰ
63. አሉም: «እነዚህ በእርግጥ ደጋሚዎች ናቸው። ከምድራችሁ በድግምታቸው ሊያወጧችሁ በላጪቱንም መንገዳችሁን ሊያስወግዱባችሁ ይሻሉ።
(63) They said, “These two are merely magicians who want to drive you out of your land with their magic and destroy your exemplary way of life.
(٦٤) فَأَجْمِعُوا كَيْدَكُمْ ثُمَّ ائْتُوا صَفًّا ۚ وَقَدْ أَفْلَحَ الْيَوْمَ مَنِ اسْتَعْلَىٰ
64. «ተንኮላችሁንም አጠንክሩ። ከዚያም ተሰልፋችሁ ኑ። ዛሬ ያሸነፈም ሰው ምኞቱን አገኘ።» ተባባሉ።
(64) So gather your scheme, then line up in a row. Whoever prevails today is indeed the victor.”
(٦٥) قَالُوا يَا مُوسَىٰ إِمَّا أَن تُلْقِيَ وَإِمَّا أَن نَّكُونَ أَوَّلَ مَنْ أَلْقَىٰ
65. «ሙሳ ሆይ! በመጀመሪያ ትጥላለህ ወይስ እኛ እንጣል? (ምረጥ)» አሉ።
(65) They said, “O Moses, either you throw or shall we be the first to throw!”
(٦٦) قَالَ بَلْ أَلْقُوا ۖ فَإِذَا حِبَالُهُمْ وَعِصِيُّهُمْ يُخَيَّلُ إِلَيْهِ مِن سِحْرِهِمْ أَنَّهَا تَسْعَىٰ
66. ሙሳም «እናንተ በመጀመሪያ ጣሉ።» አላቸው። ጣሉም። ወዲያዉም ገመዶቻቸውና ዘንጎቻቸው ከድግምታቸው የተነሳ የሚሮጡ እባቦች ሆነው (መስለው) ወደ እርሱ ተመሰሉበት።
(66) He said, “No; you throw first.” Suddenly their ropes and staffs appeared to him, owing to their magic, as if they were slithering.
(٦٧) فَأَوْجَسَ فِي نَفْسِهِ خِيفَةً مُّوسَىٰ
67.ሙሳም በውስጡ ፍርሃት አደረበት።
(67) Then Moses sensed fear within himself.
(٦٨) قُلْنَا لَا تَخَفْ إِنَّكَ أَنتَ الْأَعْلَىٰ
68. አልነውም: «አትፍራ። የበላዩ አንተ ነህና።
(68) We said, “Do not be afraid; it is you who will prevail.
(٦٩) وَأَلْقِ مَا فِي يَمِينِكَ تَلْقَفْ مَا صَنَعُوا ۖ إِنَّمَا صَنَعُوا كَيْدُ سَاحِرٍ ۖ وَلَا يُفْلِحُ السَّاحِرُ حَيْثُ أَتَىٰ
69. «በቀኝ እጅህ ያለችውን ብትር ጣል። ያንን የሰሩትን ሁሉ ትውጣለችና። ያ የሰሩት ሁሉ የድግምተኛ ተንኮል ብቻ ነውና። ድግምተኛም በመጣበት ስፍራ ሁሉ አይቀናዉም።»
(69) Throw what is in your right hand; it will swallow up what they have contrived. They have only contrived a magic trick, and the magician will never prosper, wherever he goes.”
(٧٠) فَأُلْقِيَ السَّحَرَةُ سُجَّدًا قَالُوا آمَنَّا بِرَبِّ هَارُونَ وَمُوسَىٰ
70. ድግምተኞቹም ሱጁድ ወረዱ: «በሃሩንና በሙሳ ጌታ አመንን።» አሉ።
(70) So the magicians fell down in prostration, saying, “We believe in the Lord of Aaron and Moses.”
(٧١) قَالَ آمَنتُمْ لَهُ قَبْلَ أَنْ آذَنَ لَكُمْ ۖ إِنَّهُ لَكَبِيرُكُمُ الَّذِي عَلَّمَكُمُ السِّحْرَ ۖ فَلَأُقَطِّعَنَّ أَيْدِيَكُمْ وَأَرْجُلَكُم مِّنْ خِلَافٍ وَلَأُصَلِّبَنَّكُمْ فِي جُذُوعِ النَّخْلِ وَلَتَعْلَمُنَّ أَيُّنَا أَشَدُّ عَذَابًا وَأَبْقَىٰ
71. (ፈርዖንም) «ለእናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት ለእርሱ አመናችሁለትን! እርሱ በእርግጥ ያ ድግምትን ያስተማራችሁ መሪያችሁ ነው። እጆቻችሁንና እግሮቻችሁን (በማናጋት) ግራንና ቀኝን በማፈራረቅ እቆራርጣችኋለሁ። በዘምባባም ግንዶች ላይ እሰቅላችኋለሁ። የማንኛችን ቅጣት በጣም ብርቱና የሚቆይ መሆኑን በዚያ ጊዜ ታውቃላችሁ።» አላቸው።
(71) Pharaoh said, “How dare you believe in him before I give you permission! He must be your master who taught you magic! I will surely cut off your hands and feet on opposite sides, and I will crucify you on the trunks of palm trees; you will surely know whose punishment is more severe and more lasting!”
(٧٢) قَالُوا لَن نُّؤْثِرَكَ عَلَىٰ مَا جَاءَنَا مِنَ الْبَيِّنَاتِ وَالَّذِي فَطَرَنَا ۖ فَاقْضِ مَا أَنتَ قَاضٍ ۖ إِنَّمَا تَقْضِي هَـٰذِهِ الْحَيَاةَ الدُّنْيَا
72. አሉትም: «ከመጡልን ተዓምራትና ከዚያ ከፈጠረን አምላክ ፈጽሞ አናስበልጥህም። እናም የምትፈርደውን ፍረድ። የምትፈርደው በዚህች በአነስተኛይቱ ህይወት ብቻ ላይ ነውና።
(72) They said, “We will never choose you over the clear signs that have come to us, or over the One Who created us. So decide whatever you will. You can only make a decision about the life of this world.
(٧٣) إِنَّا آمَنَّا بِرَبِّنَا لِيَغْفِرَ لَنَا خَطَايَانَا وَمَا أَكْرَهْتَنَا عَلَيْهِ مِنَ السِّحْرِ ۗ وَاللَّهُ خَيْرٌ وَأَبْقَىٰ
73. «ኃጢአቶቻችንንና ከድግምትም እንድንፈጽመው ያስገደድከንን ይምረን ዘንድ እኛ በጌታችን አምነናል። አላህ በጣም በላጭ ነው። ቅጣቱም ሆነ ምንዳው በጣም የሚዘወትር ነው።» አሉ።
(73) We surely believe in our Lord so that He may forgive us our sins and the magic that you have compelled us to practice, for Allah is best [in reward] and more lasting [in punishment].”
(٧٤) إِنَّهُ مَن يَأْتِ رَبَّهُ مُجْرِمًا فَإِنَّ لَهُ جَهَنَّمَ لَا يَمُوتُ فِيهَا وَلَا يَحْيَىٰ
74. ከሃዲ ሆኖ ወደ ጌታው የሚመጣ (የሚሞት) ሰው ሁሉ ለእርሱ ገሀነም አለችለት። በውስጧም አይሞትም ህያዉም አይሆንም።
(74) Whoever comes to his Lord as an evildoer, for him is Hell; he will neither die therein nor live.
(٧٥) وَمَن يَأْتِهِ مُؤْمِنًا قَدْ عَمِلَ الصَّالِحَاتِ فَأُولَـٰئِكَ لَهُمُ الدَّرَجَاتُ الْعُلَىٰ
75.እነዚያ በጎ ስራዎችን የሰሩና አማኝ ሆነው ወደ ጌታቸው የመጡ ሰዎች ደግሞ እነዚያ ለእነርሱ ከፍተኛ ደረጃዎች አሏቸው።
(75) But whoever comes to Him as a believer, having done righteous deeds, it is they who will have the highest ranks:
(٧٦) جَنَّاتُ عَدْنٍ تَجْرِي مِن تَحْتِهَا الْأَنْهَارُ خَالِدِينَ فِيهَا ۚ وَذَٰلِكَ جَزَاءُ مَن تَزَكَّىٰ
76.ከስሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው የመኖሪያ ገነቶች በውስጣቸው ዘውታሪዎች ሲሆኑ አሏቸው። ይህም አይነቱ ክፍያ ለተጥራራ ሁሉ ምንዳው ነው።
(76) Gardens of Eternity, under which rivers flow, abiding therein forever. Such is the reward of those who purify themselves.
(٧٧) وَلَقَدْ أَوْحَيْنَا إِلَىٰ مُوسَىٰ أَنْ أَسْرِ بِعِبَادِي فَاضْرِبْ لَهُمْ طَرِيقًا فِي الْبَحْرِ يَبَسًا لَّا تَخَافُ دَرَكًا وَلَا تَخْشَىٰ
77. ወደ ሙሳም «ባሮቼን ይዘህ በሌሊት ሂድ። ለእነርሱም በባህር ውስጥ ደረቅ መንገድን አድርግላቸው። ፈርዖን ያገኘኛል ብለህ አትፍራ። ከመስመጥም አትጨነቅ።» ስንል በእርግጥ ላክንበት።
(77) We inspired Moses, “Travel by night with My slaves, and strike for them a dry path across the sea. Have no fear of being overtaken, nor be afraid [of drowning].”
(٧٨) فَأَتْبَعَهُمْ فِرْعَوْنُ بِجُنُودِهِ فَغَشِيَهُم مِّنَ الْيَمِّ مَا غَشِيَهُمْ
78. ፈርዖን ከሰራዊቱ ጋር ሆኖ ተከተላቸው። ከባህሩም የሚሸፍን ነገር ሸፈናቸው።
(78) Then Pharaoh pursued them with his soldiers, but they were completely overwhelmed by the sea.
(٧٩) وَأَضَلَّ فِرْعَوْنُ قَوْمَهُ وَمَا هَدَىٰ
79.ፈርዖንም ህዝቦቹን አሳሳታቸው። ቅኑንም መንገድ አልመራቸዉም።
(79) Thus Pharaoh led his people astray, and did not guide them.
(٨٠) يَا بَنِي إِسْرَائِيلَ قَدْ أَنجَيْنَاكُم مِّنْ عَدُوِّكُمْ وَوَاعَدْنَاكُمْ جَانِبَ الطُّورِ الْأَيْمَنَ وَنَزَّلْنَا عَلَيْكُمُ الْمَنَّ وَالسَّلْوَىٰ
80. የኢስራኢል ልጆች ሆይ! ከጠላታችሁ በእርግጥ አዳንናችሁ። በጡር ተራራም ቀኝ ጎን ላይ ቀጠሮ አደረግንላችሁ። በእናንተም ላይ መናንና ሰልዋን (ድርጭት) አወረድንላችሁ።
(80) O Children of Israel, We rescued you from your enemy, and made an appointment with you on the right side of Mount Tūr [in Sinai], and sent down for you manna and quails,
(٨١) كُلُوا مِن طَيِّبَاتِ مَا رَزَقْنَاكُمْ وَلَا تَطْغَوْا فِيهِ فَيَحِلَّ عَلَيْكُمْ غَضَبِي ۖ وَمَن يَحْلِلْ عَلَيْهِ غَضَبِي فَقَدْ هَوَىٰ
81. ከሰጠናችሁ ሲሳይ ከመልካሙ ብሉ። በእርሱም ወሰንን አትለፉ። ቁጣዬ በእናንተ ላይ ይወርድባችኋልና። ቁጣዬ የሚወርድበት ሁሉ በእርግጥ ይጠፋል።
(81) [saying], “Eat from the good things We have provided for you, but do not exceed the limits therein, or My wrath will befall you, for anyone upon whom My wrath befalls is perished.
(٨٢) وَإِنِّي لَغَفَّارٌ لِّمَن تَابَ وَآمَنَ وَعَمِلَ صَالِحًا ثُمَّ اهْتَدَىٰ
82.እኔም ለተጸጸተ ላመነም መልካምንም ለሰራ ከዚያ ለተመራ ሁሉ በእርግጥ መሓሪ ነኝ።
(82) I am indeed Most Forgiving to those who repent and believe, and do righteous deeds, then stay on the right path.”
(٨٣) وَمَا أَعْجَلَكَ عَن قَوْمِكَ يَا مُوسَىٰ
83. «ሙሳ ሆይ! ከህዝቦችህ ምን አስቸኮለህ?» ተባለ።
(83) [Allah asked], “What made you hasten from your people, O Moses?”
(٨٤) قَالَ هُمْ أُولَاءِ عَلَىٰ أَثَرِي وَعَجِلْتُ إِلَيْكَ رَبِّ لِتَرْضَىٰ
84. «እነርሱ እነዚህ በዱካዬ ላይ ያሉ ናቸው። ጌታዬ ሆይ! ትወድልኝ ዘንድ ወደ አንተ ቸኮልኩ።» አለ።
(84) He said, “They are following my footsteps; I hastened to You, my Lord, to please You.”
(٨٥) قَالَ فَإِنَّا قَدْ فَتَنَّا قَوْمَكَ مِن بَعْدِكَ وَأَضَلَّهُمُ السَّامِرِيُّ
85.(አላህም) «እኛም ካንተ በኋላ ሰዎችህን በእርግጥ ፈተንን። ሳምራዊዉም አሳሳታቸው።» አለው።
(85) Allah said, “We have certainly tested your people in your absence, and Sāmiri has led them astray.”
(٨٦) فَرَجَعَ مُوسَىٰ إِلَىٰ قَوْمِهِ غَضْبَانَ أَسِفًا ۚ قَالَ يَا قَوْمِ أَلَمْ يَعِدْكُمْ رَبُّكُمْ وَعْدًا حَسَنًا ۚ أَفَطَالَ عَلَيْكُمُ الْعَهْدُ أَمْ أَرَدتُّمْ أَن يَحِلَّ عَلَيْكُمْ غَضَبٌ مِّن رَّبِّكُمْ فَأَخْلَفْتُم مَّوْعِدِي
86. ሙሳም ወደ ሰዎች የተቆጣና ያዘነ ሆኖ ተመለሰ። «ህዝቦቼ ሆይ! ጌታችሁ መልካም ተስፋን አልቀጠራችሁምን? ቀጠሮው በእናንተ ላይ ረዘመባችሁን? ወይስ በእናንተ ላይ ከጌታችሁ ቅጣት ሊወርድባችሁ ፈለጋችሁና ቃል ኪዳኔን አፈረሳችሁ?» አላቸው።
(86) So Moses returned to his people, angry and sorrowful. He said, “O my people, did your Lord not promise you a good promise? Was my absence too long for you, or did you want the wrath from your Lord to befall you, so you broke your promise to me?”
(٨٧) قَالُوا مَا أَخْلَفْنَا مَوْعِدَكَ بِمَلْكِنَا وَلَـٰكِنَّا حُمِّلْنَا أَوْزَارًا مِّن زِينَةِ الْقَوْمِ فَقَذَفْنَاهَا فَكَذَٰلِكَ أَلْقَى السَّامِرِيُّ
87. «ቀጠሮህን በፈቃዳችን አልጣስንም። ግን እኛ ከህዝቦች ጌጥ ሸክሞችን ተጫን። በእሳት ላይ ጣልናትም። ሳምራዊዉም እንደዚሁ አብሮን ጣለ።» አሉት።
(87) They said, “We did not break our promise to you out of our own free will, but we were made to carry loads of the people’s jewelry, so we threw them [into the fire], and so did the Sāmiri throw.”
(٨٨) فَأَخْرَجَ لَهُمْ عِجْلًا جَسَدًا لَّهُ خُوَارٌ فَقَالُوا هَـٰذَا إِلَـٰهُكُمْ وَإِلَـٰهُ مُوسَىٰ فَنَسِيَ
88. ለእነርሱም የመጓጎር ባህሪ ያለውን ጥጃን (መሰል) አካልን አወጣላቸው። «ተከታዮቹ ሆይ! ይህ የእናንተም ሆነ የሙሳ አምላክ ነው። ግን ረሳው እንጂ።» አሉ።
(88) Then he moulded for them an image of a calf that made a mooing sound. They said, “This is your god and Moses’ god, but he has forgotten.”
(٨٩) أَفَلَا يَرَوْنَ أَلَّا يَرْجِعُ إِلَيْهِمْ قَوْلًا وَلَا يَمْلِكُ لَهُمْ ضَرًّا وَلَا نَفْعًا
89.ወደ እነርሱ ንግግርን የማይመልስ ለእነርሱም ጉዳትንና ጥቅምን የማይችል መሆኑን አያዩምን?
(89) Do they not see that it does not respond a word to them, nor does it have power to harm or benefit them?
(٩٠) وَلَقَدْ قَالَ لَهُمْ هَارُونُ مِن قَبْلُ يَا قَوْمِ إِنَّمَا فُتِنتُم بِهِ ۖ وَإِنَّ رَبَّكُمُ الرَّحْمَـٰنُ فَاتَّبِعُونِي وَأَطِيعُوا أَمْرِي
90-.ከዚያ በፊት ሀሩንም በእርግጥ አላቸው: «ህዝቦቼ ሆይ! ይህ በእርሱ የተሞከራችሁበት ብቻ ነው። ጌታችሁም አር-ረህማን ነው። ተከተሉኝም፤ ትእዛዜንም ስሙ።»
(90) Aaron told them beforehand, “O my people, you are being tested with it. Your Lord is the Most Compassionate, so follow me and obey my command.”
(٩١) قَالُوا لَن نَّبْرَحَ عَلَيْهِ عَاكِفِينَ حَتَّىٰ يَرْجِعَ إِلَيْنَا مُوسَىٰ
91. «ሙሳ ወደ እኛ እስከሚመለስ በእርሱ መገዛት ላይ ከመቆየት ፈጽሞ አንወገድም።» አሉ።
(91) They said, “We will never cease to worship it until Moses comes back to us.”
(٩٢) قَالَ يَا هَارُونُ مَا مَنَعَكَ إِذْ رَأَيْتَهُمْ ضَلُّوا
92- ሙሳም አለ፡- «ሃሩን ሆይ! ተሳስተው ባየሃቸው ጊዜ ምን ከለከለህ?
(92) Moses said, “O Aaron, what prevented you when you saw them going astray,
(٩٣) أَلَّا تَتَّبِعَنِ ۖ أَفَعَصَيْتَ أَمْرِي
93. «እኔን ከመከተል? ትእዛዜን ጣስክን?» አለ።
(93) from following me? Did you disobey my command?”
(٩٤) قَالَ يَا ابْنَ أُمَّ لَا تَأْخُذْ بِلِحْيَتِي وَلَا بِرَأْسِي ۖ إِنِّي خَشِيتُ أَن تَقُولَ فَرَّقْتَ بَيْنَ بَنِي إِسْرَائِيلَ وَلَمْ تَرْقُبْ قَوْلِي
94. «ሃሩን የእናቴ ልጅ ሆይ! ፂሜንም ሆነ ራሴን አትያዝ። እኔ ‹በኢስራኢል ልጆች መካከል ለያየህ ቃሌንም አልጠበክም› ማለትህን ፈራሁና ነው።» አለው።
(94) Aaron said, “O son of my mother, do not seize me by my beard or by my head! I feared that you would say, ‘You have caused division among the Children of Israel, and did not heed my words.’”
(٩٥) قَالَ فَمَا خَطْبُكَ يَا سَامِرِيُّ
95. ሙሳም «ሳምራዊው ሆይ! ነገርህ ምንድን ነው?» አለ።
(95) Moses said, “What is the matter with you, O Sāmiri?”
(٩٦) قَالَ بَصُرْتُ بِمَا لَمْ يَبْصُرُوا بِهِ فَقَبَضْتُ قَبْضَةً مِّنْ أَثَرِ الرَّسُولِ فَنَبَذْتُهَا وَكَذَٰلِكَ سَوَّلَتْ لِي نَفْسِي
96. ሳምራዊውም: «እነርሱ ያላዩትን ነገር አየሁ። ከመልዕክተኛው ፈረስ ኮቴ ዱካም ጭብጥ አፈርን ዘገንኩ። በቅርጹ ላይ ጣልኳትም። ልክ እንደዚሁ ነፍሴ ሸለመችልኝ።» አለ።
(96) He said, “I saw something they did not see, so I took a handful [of dust] from the hoof-print of the horse of the messenger [Gabriel] and cast it [into the fire]. This is what my mind prompted me.”
(٩٧) قَالَ فَاذْهَبْ فَإِنَّ لَكَ فِي الْحَيَاةِ أَن تَقُولَ لَا مِسَاسَ ۖ وَإِنَّ لَكَ مَوْعِدًا لَّن تُخْلَفَهُ ۖ وَانظُرْ إِلَىٰ إِلَـٰهِكَ الَّذِي ظَلْتَ عَلَيْهِ عَاكِفًا ۖ لَّنُحَرِّقَنَّهُ ثُمَّ لَنَنسِفَنَّهُ فِي الْيَمِّ نَسْفًا
97. ሙሳም ለሳምራዊው አለው: «ሂድ። በህይወትህ ላየኸው ሰው ሁሉ ‹መነካካት የለም› እያልክ ኑር። ላንተም ፈጽሞ የማትቀር ቀጠሮ አለህ። ወደ እዚያዉም በእርሱ ላይ ተገዢው ሆነህ ወደ ቆየህበት አምላክህ ተመልከት። በእርግጥ እናቃጥለዋለን። ከዚያም በባህሩ ውስጥ እንበትነዋለን።»
(97) Moses said, “Begone then! Your [punishment] in this life will be to say, ‘Do not touch me,’ but there awaits you an appointed time for your reckoning that you cannot escape. Now look at your so-called god which you kept worshiping; We will surely burn it then scatter it in the sea.
(٩٨) إِنَّمَا إِلَـٰهُكُمُ اللَّهُ الَّذِي لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۚ وَسِعَ كُلَّ شَيْءٍ عِلْمًا
98.(ሰዎች ሆይ!) ጌታችሁም ያ ከእርሱ በስተቀር ሌላ አምላክ የሌለ የሆነው አላህ ብቻ ነው። እውቀቱ ሁሉን ነገር አዳረሰ።
(98) [O people], your god is only Allah; none has the right to be worshiped except Him. He encompasses everything in knowledge.”
(٩٩) كَذَٰلِكَ نَقُصُّ عَلَيْكَ مِنْ أَنبَاءِ مَا قَدْ سَبَقَ ۚ وَقَدْ آتَيْنَاكَ مِن لَّدُنَّا ذِكْرًا
99. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ልክ እንደዚሁ በእርግጥ ካለፉት ወሬዎች ባንተ ላይ እንተርካለን፤ ከእኛም ዘንድ ቁርኣንን በእርግጥ ሰጠንህ።
(99) This is how We relate to you [O Prophet] from the stories of the past, and We have given you a Reminder from Us.
(١٠٠) مَّنْ أَعْرَضَ عَنْهُ فَإِنَّهُ يَحْمِلُ يَوْمَ الْقِيَامَةِ وِزْرًا
100.ከእርሱ ያፈገፈገ ሰው እርሱ በትንሳኤ ቀን ከባድን ቅጣት ይሸከማል።
(100) Whoever turns away from it will bear a heavy burden on the Day of Resurrection,
(١٠١) خَالِدِينَ فِيهِ ۖ وَسَاءَ لَهُمْ يَوْمَ الْقِيَامَةِ حِمْلًا
101.በእርሱ ውስጥ ዘውታሪዎች ሆነው ይሸከማሉ። በትንሳኤ ቀን ለእነርሱ እጣ ፈንታ የሆነው ሸክም ከፋ!
(101) abiding therein forever. What a terrible burden they will carry on the Day of Resurrection!
(١٠٢) يَوْمَ يُنفَخُ فِي الصُّورِ ۚ وَنَحْشُرُ الْمُجْرِمِينَ يَوْمَئِذٍ زُرْقًا
102. በቀንዱ በሚነፋ ቀን ሸክማቸው ከፋ። ከሓዲያን በዚያ ቀን ዓይኖቻቸው ሰማያዊዎች ሆነው እንሰበስባቸዋለን።
(102) the Day when the Trumpet will be blown; on that Day We will gather together the wicked sightless [from horror].
(١٠٣) يَتَخَافَتُونَ بَيْنَهُمْ إِن لَّبِثْتُمْ إِلَّا عَشْرًا
103. «አስርን (ቀን) እንጂ አልቆያችሁም።» በመባባል በመካከላቸው ይንሾካሾካሉ።
(103) They will whisper with one another, “You stayed no more than ten days [on earth].”
(١٠٤) نَّحْنُ أَعْلَمُ بِمَا يَقُولُونَ إِذْ يَقُولُ أَمْثَلُهُمْ طَرِيقَةً إِن لَّبِثْتُمْ إِلَّا يَوْمًا
104. በሃሳብ ቀጥተኛቸው «አንድን ቀን እንጂ አልቆያችሁም።» በሚል ጊዜ የሚሉትን ነገር እኛ አዋቂዎች ነን።
(104) We know best what they will say – the most discerning among them will say, “You stayed no more than a day.”
(١٠٥) وَيَسْأَلُونَكَ عَنِ الْجِبَالِ فَقُلْ يَنسِفُهَا رَبِّي نَسْفًا
105. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከጋራዎች ይጠይቁሃልና (እንዲህ) በላቸው: «ጌታዬ መበተንን ይበትናቸዋል።
(105) They ask you about the mountains, say, “My Lord will scatter them into dust,
(١٠٦) فَيَذَرُهَا قَاعًا صَفْصَفًا
106. «ትክክል ሜዳም ሆና ይተዋታል።
(106) and He will leave the earth level and plain,
(١٠٧) لَّا تَرَىٰ فِيهَا عِوَجًا وَلَا أَمْتًا
107. «በእርሷ ዝቅታና ከፍታን ፈጽሞ አታይም።»
(107) you will not see therein any troughs or peaks.”
(١٠٨) يَوْمَئِذٍ يَتَّبِعُونَ الدَّاعِيَ لَا عِوَجَ لَهُ ۖ وَخَشَعَتِ الْأَصْوَاتُ لِلرَّحْمَـٰنِ فَلَا تَسْمَعُ إِلَّا هَمْسًا
108. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በዚያ ቀን ለመሰብሰብ ጠሪውን ምንም እንከን የሌለውን ተጣሪ ይከተላሉ። ድምፆችም ሁሉ ለአር-ረህማን ጸጥ ይላሉ። ስለዚህ (የኮቴ) ሹክሹክታን እንጂ አትሰማም።
(108) On that day, they will follow the summoner; none will dare to deviate. All voices will be hushed in awe before the Most Compassionate; you will hear nothing except a whisper.
(١٠٩) يَوْمَئِذٍ لَّا تَنفَعُ الشَّفَاعَةُ إِلَّا مَنْ أَذِنَ لَهُ الرَّحْمَـٰنُ وَرَضِيَ لَهُ قَوْلًا
109.በዚያ ቀን ለእርሱ አር-ረህማን የፈቀደለትንና ለእርሱም ቃልን የወደደለትን ብቻ ቢሆን እንጂ ምልጃ አንድንም አትጠቅምም።
(109) On that day, no intercession will be of any use except to whom the Most Compassionate gave permission and approved his word.
(١١٠) يَعْلَمُ مَا بَيْنَ أَيْدِيهِمْ وَمَا خَلْفَهُمْ وَلَا يُحِيطُونَ بِهِ عِلْمًا
110. በስተፊታቸው ያለውንም ሆነ በስተኋላቸው ያለውን ሁሉ ያውቃል። በእርሱ ላይ ግን ማንም በእውቀቱ አያካብብም።
(110) He knows all that is ahead of them and all that is behind them, but they do not encompass it with their knowledge.
(١١١) وَعَنَتِ الْوُجُوهُ لِلْحَيِّ الْقَيُّومِ ۖ وَقَدْ خَابَ مَنْ حَمَلَ ظُلْمًا
111. ፊቶችም ሁሉ ህያውና የሁሉ አስተናባሪ ለሆነው አላህ ተዋረዱ። በደልንም የተሸከመ በእርግጥ ከሰረ።
(111) All faces will be humbled before the Ever-Living, Self-Sustaining. Those burdened with evil deeds will be in total loss.
(١١٢) وَمَن يَعْمَلْ مِنَ الصَّالِحَاتِ وَهُوَ مُؤْمِنٌ فَلَا يَخَافُ ظُلْمًا وَلَا هَضْمًا
112. አማኝ ሆኖ መልካም ስራዎችን የሰራ በደልንም ሆነ መጉደልን አይፈራም።
(112) But whoever does righteous deeds, being a believer, will have no fear of being wronged or deprived.
(١١٣) وَكَذَٰلِكَ أَنزَلْنَاهُ قُرْآنًا عَرَبِيًّا وَصَرَّفْنَا فِيهِ مِنَ الْوَعِيدِ لَعَلَّهُمْ يَتَّقُونَ أَوْ يُحْدِثُ لَهُمْ ذِكْرًا
113.ልክ እንደዚሁም ዐረብኛ ቁርኣን ሆኖ አወረድነው። አላህን ይፈሩ ዘንድ ወይም ለእነርሱ ግሣጼን ያድስላቸው ዘንድ ከዛቻ ደጋግመን በውስጡ ገለጽን።
(113) We have sent it down as an Arabic Qur’an and diversified its warnings, so that they may fear Allah or it may cause them to take heed.
(١١٤) فَتَعَالَى اللَّهُ الْمَلِكُ الْحَقُّ ۗ وَلَا تَعْجَلْ بِالْقُرْآنِ مِن قَبْلِ أَن يُقْضَىٰ إِلَيْكَ وَحْيُهُ ۖ وَقُل رَّبِّ زِدْنِي عِلْمًا
114. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እውነተኛው ንጉስ አላህ ከሓዲያን ከሚሉት ነገር ሁሉ ላቀ። ወደ አንተ መወረዱም ከመፈጸሙ በፊት ቁርኣንን በማንበብ አትቸኩል። «ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ጨምርልኝ።» በልም።
(114) So Exalted is Allah, the True Sovereign. Do not hasten to [recite] the Qur’an before its revelation to you is concluded, and say, “My Lord, increase me in knowledge.”
(١١٥) وَلَقَدْ عَهِدْنَا إِلَىٰ آدَمَ مِن قَبْلُ فَنَسِيَ وَلَمْ نَجِدْ لَهُ عَزْمًا
115. ወደ አደምም ከዚህ በፊት ቃል ኪዳንን በእርግጥ አወረድንና ረሳ። ለእርሱም ቆራጥነትን አላገኘንለትም።
(115) We had already given a command to Adam before, but he forgot, and We found him lacking a firm resolve.
(١١٦) وَإِذْ قُلْنَا لِلْمَلَائِكَةِ اسْجُدُوا لِآدَمَ فَسَجَدُوا إِلَّا إِبْلِيسَ أَبَىٰ
116.(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ለመላእክትም «ለአደም ስገዱ።» ባልን ጊዜ (የሆነውን አስታውስ)። እነርሱም ዲያብሎስ ብቻ ሲቀር ሰገዱ። እሱማ እምቢ አለ።
(116) When We said to the angels, “Prostrate before Adam,” so they all prostrated, except Iblīs, who refused.
(١١٧) فَقُلْنَا يَا آدَمُ إِنَّ هَـٰذَا عَدُوٌّ لَّكَ وَلِزَوْجِكَ فَلَا يُخْرِجَنَّكُمَا مِنَ الْجَنَّةِ فَتَشْقَىٰ
117.ከዚያም አልን: «አደም ሆይ! ይህ ላንተም ለሚስትህም በእርግጥ ጠላት ነው። ስለዚህ ከገነት አያውጣችሁ፤ ትለፋለህና።
(117) We said “O Adam, this is an enemy to you and to your wife, so do not let him drive you both out of Paradise, for then you will fall into misery.
(١١٨) إِنَّ لَكَ أَلَّا تَجُوعَ فِيهَا وَلَا تَعْرَىٰ
118.(አደም ሆይ!) «ላንተ በእርሷ ውስጥ አለመራብና አለመታረዝ አለህ።
(118) Here you will neither go hungry nor naked,
(١١٩) وَأَنَّكَ لَا تَظْمَأُ فِيهَا وَلَا تَضْحَىٰ
119. «አንተም ከእርሷ ውስጥ አትጠማም። በጸሐይም አትተኮስም።»
(119) nor will you suffer from thirst or from scorching heat.”
(١٢٠) فَوَسْوَسَ إِلَيْهِ الشَّيْطَانُ قَالَ يَا آدَمُ هَلْ أَدُلُّكَ عَلَىٰ شَجَرَةِ الْخُلْدِ وَمُلْكٍ لَّا يَبْلَىٰ
120. ሰይጣን ወደ እርሱ (አደም) « አደም ሆይ! በመዘውተሪያ ዛፍ በማይጠፋ ንግስናም ላይ ላመላክትህን?» በማለት ጎተጎተ።
(120) Then Satan whispered to him, and said, “O Adam, shall I show you the tree of immortality and a kingdom that will never decay?”
(١٢١) فَأَكَلَا مِنْهَا فَبَدَتْ لَهُمَا سَوْآتُهُمَا وَطَفِقَا يَخْصِفَانِ عَلَيْهِمَا مِن وَرَقِ الْجَنَّةِ ۚ وَعَصَىٰ آدَمُ رَبَّهُ فَغَوَىٰ
121.ከእርሷም በሉ። ለእነርሱም ሀፍረተ ገላቸው ተገለጸች። ከገነትም ቅጠል በላያቸው ላይ ይለጥፉ ጀመር። አደምም የጌታውን ትእዛዝ ረስቶ ጣሰ። ተሳሳተም።
(121) So they both ate from the tree, then their nakedness was revealed to each other, and they began to put together leaves from Paradise to cover themselves. Thus Adam disobeyed his Lord, and fell into error.
(١٢٢) ثُمَّ اجْتَبَاهُ رَبُّهُ فَتَابَ عَلَيْهِ وَهَدَىٰ
122. ከዚያም ጌታው መረጠው። ከእርሱም ጸጸቱን ተቀበለው። መራዉም።
(122) Thereafter his Lord chose him, accepted his repentance, and guided him.
(١٢٣) قَالَ اهْبِطَا مِنْهَا جَمِيعًا ۖ بَعْضُكُمْ لِبَعْضٍ عَدُوٌّ ۖ فَإِمَّا يَأْتِيَنَّكُم مِّنِّي هُدًى فَمَنِ اتَّبَعَ هُدَايَ فَلَا يَضِلُّ وَلَا يَشْقَىٰ
123.አላህም አላቸው፡- «ከፊላችሁ ለከፊሉ ጠላት ሲሆን (አደምና ሐዋ) ሁላችሁም ከእርሷ ውረዱ። ከእኔ የሆነ መመሪያ ቢመጣላችሁ መመሪያየን የተከተለ ሁሉ አይሳሳትም። አይቸገርምም።
(123) Allah said, “Get down, both of you, from here altogether [with Satan] as enemies to one another. Then when there comes to you guidance from Me, whoever follows My guidance will neither go astray nor fall into misery.
(١٢٤) وَمَنْ أَعْرَضَ عَن ذِكْرِي فَإِنَّ لَهُ مَعِيشَةً ضَنكًا وَنَحْشُرُهُ يَوْمَ الْقِيَامَةِ أَعْمَىٰ
124. «ከግሳጼዬ የዞረ ግን በዚህች ዓለም ጠባብ ኑሮ አለው። በትንሳኤ ቀንም ዕውር ሆኖ እንቀሰቅሰዋለን።»
(124) But whoever turns away from My Reminder will have a miserable life, and on the Day of Resurrection We will raise him blind.”
(١٢٥) قَالَ رَبِّ لِمَ حَشَرْتَنِي أَعْمَىٰ وَقَدْ كُنتُ بَصِيرًا
125. «ጌታዬ ሆይ! ለምን ዕውር አድርገህ አስነሳኸኝ። በእርግጥ የማይ የነበርኩ ስሆን» አለ።
(125) He will say, “My Lord, why have you raised me blind, when I was able to see before?”
(١٢٦) قَالَ كَذَٰلِكَ أَتَتْكَ آيَاتُنَا فَنَسِيتَهَا ۖ وَكَذَٰلِكَ الْيَوْمَ تُنسَىٰ
126. «ነገሩ ልክ እንደዚሁ ነው። ተዓምራቶቻችን መጡልህና ተውካቸውም። ልክ እንደዚሁም ዛሬ ትተዋለህ።» ይለዋል።
(126) Allah will say, “Similarly Our verses came to you, but you ignored them, so you will be ignored Today.”
(١٢٧) وَكَذَٰلِكَ نَجْزِي مَنْ أَسْرَفَ وَلَمْ يُؤْمِن بِآيَاتِ رَبِّهِ ۚ وَلَعَذَابُ الْآخِرَةِ أَشَدُّ وَأَبْقَىٰ
127.እንደዚሁም ያጋራንና በጌታው አናቅጽ ያላመነን እንቀጣዋለን። የመጨረሻይቱ ዓለም ቅጣት በጣም ብርቱና ለሁልጊዜም ዘውታሪ ነው።
(127) This is how We recompense those who transgress the limits and do not believe in the verses of his Lord; and the punishment of the Hereafter is more severe and more lasting.
(١٢٨) أَفَلَمْ يَهْدِ لَهُمْ كَمْ أَهْلَكْنَا قَبْلَهُم مِّنَ الْقُرُونِ يَمْشُونَ فِي مَسَاكِنِهِمْ ۗ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَاتٍ لِّأُولِي النُّهَىٰ
128. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! ቁረይሾች) ከእነርሱ በፊት ከክፍለ ዘመናት ህዝቦች ብዙዎችን ያጠፋን መሆናችን በመኖሪያዎቻቸው የሚሄዱ ሆነው ሳሉ ለእነርሱ አልተገለጸላቸዉምን? በዚህ ውስጥ ለአእምሮ ባለቤቶች በእርግጥ መልዕክቶች አሉበት።
(128) Is it not yet clear to them how many generations We destroyed before them, in whose dwellings they still walk about? There are signs in this for people of sound intellect.
(١٢٩) وَلَوْلَا كَلِمَةٌ سَبَقَتْ مِن رَّبِّكَ لَكَانَ لِزَامًا وَأَجَلٌ مُّسَمًّى
129.(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከጌታህ ያለፈች ቃልና የተወሰነ ጊዜ ባልነበረ ኖሮ ቅጣቱ አሁኑኑ የሚይዛቸው ይሆን ነበር።
(129) Were it not for a prior decree from your Lord [O Prophet] and a time already set, they would have already been punished.
(١٣٠) فَاصْبِرْ عَلَىٰ مَا يَقُولُونَ وَسَبِّحْ بِحَمْدِ رَبِّكَ قَبْلَ طُلُوعِ الشَّمْسِ وَقَبْلَ غُرُوبِهَا ۖ وَمِنْ آنَاءِ اللَّيْلِ فَسَبِّحْ وَأَطْرَافَ النَّهَارِ لَعَلَّكَ تَرْضَىٰ
130. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! ) በሚሉትም ሁሉ ላይ ታገሥ፤ ጌታህንም ጸሐይ ከመውጣቷ በፊትና ከመግባቷም በፊት የምታመሰግን ሆነህ አጥራው። ከሌሊት ሰዓቶችም በቀን ጫፎችም አጥራው። በሚሰጥህ ምንዳ ልትወድ ይከጀላልና።
(130) So be patient with what they say, and glorify your Lord with praise before sunrise and before sunset, and glorify Him during the night and at both ends of the day, so that you may be pleased [with the reward].
(١٣١) وَلَا تَمُدَّنَّ عَيْنَيْكَ إِلَىٰ مَا مَتَّعْنَا بِهِ أَزْوَاجًا مِّنْهُمْ زَهْرَةَ الْحَيَاةِ الدُّنْيَا لِنَفْتِنَهُمْ فِيهِ ۚ وَرِزْقُ رَبِّكَ خَيْرٌ وَأَبْقَىٰ
131.ዐይኖችህን ከሰዎች የተወሰኑ ክፍሎችን ልንፈትናቸው ወደ አጣቀምንበት ወደ ቅርቢቱ ህይወት ጌጦች አትዘርጋ። የጌታህ ሲሳይ በጣም በላጭና ዘውታሪ ነው።
(131) Do not turn your eyes covetously towards the various forms of splendor of this life that We have given some of the [disbelievers] to enjoy, as a trial for them. But the provision of your Lord is far better and more lasting.
(١٣٢) وَأْمُرْ أَهْلَكَ بِالصَّلَاةِ وَاصْطَبِرْ عَلَيْهَا ۖ لَا نَسْأَلُكَ رِزْقًا ۖ نَّحْنُ نَرْزُقُكَ ۗ وَالْعَاقِبَةُ لِلتَّقْوَىٰ
132.(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ቤተሰብህንም በሶላት ላይ እዘዝ። አንተም በእርሷ ላይ ዘውትር። ሲሳይን አንጠይቅህም። እኛ እንሰጥሃለን። መልካሚቱ መጨረሻ ለጥንቁቆቹ ናት።
(132) Enjoin your household to perform prayer and adhere to it firmly. We ask no provision from you; rather, it is We Who give you provision. And the best outcome is for those who fear Allah.
(١٣٣) وَقَالُوا لَوْلَا يَأْتِينَا بِآيَةٍ مِّن رَّبِّهِ ۚ أَوَلَمْ تَأْتِهِم بَيِّنَةُ مَا فِي الصُّحُفِ الْأُولَىٰ
133. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ተከራካሪዎችህ «ከጌታው በሆነ ተዓምር አይመጣምን?» አሉ። በመጀመሪያዎቹ ጹሁፎች ውስጥ ያለችው ማስረጃ አልመጣቻቸዉምን?
(133) They say, “Why does he not bring us a sign from his Lord?” Has there not come to them [the Qur’an as] a confirmation of what is in the earlier Scriptures?
(١٣٤) وَلَوْ أَنَّا أَهْلَكْنَاهُم بِعَذَابٍ مِّن قَبْلِهِ لَقَالُوا رَبَّنَا لَوْلَا أَرْسَلْتَ إِلَيْنَا رَسُولًا فَنَتَّبِعَ آيَاتِكَ مِن قَبْلِ أَن نَّذِلَّ وَنَخْزَىٰ
134. እኛም (ከሙሐመድ መላክ) በፊት በቅጣት ባጠፋናቸው ኖሮ «ጌታችን ሆይ! ከመዋረዳችንና ከማፈራችን በፊት አናቅጽህን እንከተል ዘንድ ወደኛ መልዕክተኛን አትልክልንም ነበርን?» ባሉ ነበር።
(134) If We had destroyed them with a punishment before this, they would have said, “Our Lord, if only You had sent us a messenger so that we would have followed Your verses before being humiliated and disgraced.”
(١٣٥) قُلْ كُلٌّ مُّتَرَبِّصٌ فَتَرَبَّصُوا ۖ فَسَتَعْلَمُونَ مَنْ أَصْحَابُ الصِّرَاطِ السَّوِيِّ وَمَنِ اهْتَدَىٰ
135. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «ሁሉም ተጠባባቂ ነው። ተጠባበቁም የቀጥታዉም መንገድ ባለቤቶች እነማን እንደ ሆኑ እነማንም እንደ ተመሩ ወደፊት ታውቃላችሁ።» በላቸው።
(135) Say, “Each of us is waiting, so wait! You will come to know who are the people of the straight path and who are rightly guided.”
Tags: Amharic Quran Free Amharic Quran quran amharic quran in amharic ምዕራፍ 2 ሱረቱ ተባረክ ሱረቱ አል ሐጅ ሱረቱ አል ከህፍ ሱረቱ አትተውባ ሱረቱ ጡር ሱረቱል ሙልክ ሱረቱል በቀራህ ሱረቱል አል ማዒዳህ ሱረቱል አል-በቀራህ ሱረቱል ከህፍ ቁራን በአማርኛ ቁራን በአማርኛ ትርጉም ቁርአን በአማርኛ ቅዱስ ቁርአን አልበቀራህ አማርኛ ቁርአን አማርኛ ቅዱስ ቁርአን

Post navigation

❮ Previous Post: 19 Maryam
Next Post: 21 – Al-Anbiyaa ❯

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ሁሉም ሱራዎች / All Chapters

  1. ሱረቱ አል-ፋቲሃ – Al-Fātihah
  2. ሱረቱ አል-በቀራህ – Al-Baqarah
  3. ሱረቱ ኣሊ-ዒምራን – Āl-‘Imrān
  4. ሱረቱ አን-ኒሳዕ – An-Nisā’
  5. ሱረቱ አል-ማኢዳህ – Al-Mā’idah
  6. ሱረቱ አል-አንዓም – Al-An‘ām
  7. ሱረቱ አል-አዕራፍ – Al-A‘rāf
  8. ሱረቱ አል-አንፋል – Al-Anfāl
  9. ሱረቱ አት-ተውባህ – At-Tawbah
  10. ሱረቱ ዩኑስ – Yūnus
  11. ሱረቱ ሁድ – Hūd
  12. ሱረቱ ዩኑስ – Yūsuf
  13. ሱረቱ አር-ረዕድ – Ar-Ra‘d
  14. ሱረቱ ኢብራሂም – Ibrāhīm
  15. ሱረቱ አል ሒጅር – Al-Hijr
  16. ሱረቱ አን–ነሕል – An-Nahl
  17. ሱረቱ አል ኢስራዕ – Al-Isrā’
  18. ሱረቱ አል ከህፍ – Al-Kahf
  19. ሱረቱ መርየም – Maryam
  20. ሱረቱ ጣሃ – Tā-ha
  21. ሱረቱ አል አንቢያ – Al-Anbiyā’
  22. ሱረቱ አል ሐጅ – Al-Hajj
  23. ሱረቱ አል–ሙዕሚኑን – Al-Mu’minūn
  24. ሱረቱ አልን ኑር – An-Noor
  25. ሱረቱ አል ፉርቃን – Al-Furqān
  26. ሱረቱ አሽ ሹዐራእ – Ash-Shu‘arā’
  27. ሱረቱ አን ነምል – An-Naml
  28. ሱረቱ አል ቀሰስ – Al-Qasas
  29. ሱረቱ አል ዐንከቡት – Al-‘Ankabūt
  30. ሱረቱ አር ሩም – Ar-Rūm
  31. ሱረቱ አል ሉቅማን – Luqmān
  32. ሱረቱ አስ ሰጅደህ – As-Sajdah
  33. ሱረቱ አል አሕዛብ – Al-Ahzāb
  34. ሱረቱ ሰበእ – Saba’
  35. ሱረቱ ፋጢር – Fātir
  36. ሱረቱ ያሲን – Yā-Sīn
  37. ሱረቱ አስ ሷፋት – As-Sāffāt
  38. ሱረቱ ሷድ – Sād
  39. ሱረቱ አዝ ዙመር – Az-Zumar
  40. ሱረቱ ጋፊር – Ghāfir
  41. ሱረቱ ፉሲለት – Fussilat
  42. ሱረቱ አሽ ሹራ – Ash-Shūra
  43. ሱረቱ አዝ ዙኽሩፍ – Az-Zukhruf
  44. ሱረቱ አድ ዱኻን – Ad-Dukhān
  45. ሱረቱ አል ጃሲያህ – Al-Jāthiyah
  46. ሱረቱ አል አህቃፍ – Al-Ahqāf
  47. ሱረቱ ሙሐመድ – Muhammad
  48. ሱረቱ አል ፈትህ – Al-Fat’h
  49. ሱረቱ አል ሑጅራት – Al-Hujurāt
  50. ሱረቱ ቃፍ – Qāf
  51. ሱረቱ አዝ ዛሪያት – Adh-Dhāriyāt
  52. ሱረቱ አጥ ጡር – At-Toor
  53. ሱረቱ አን ነጅም – An-Najm
  54. ሱረቱ አል ቀመር – Al-Qamar
  55. ሱረቱ አር ረሕማን – Ar-Rahmān
  56. ሱረቱ አል ዋቂዓህ – Al-Wāqi‘ah
  57. ሱረቱ አል ሐዲድ – Al-Hadīd
  58. ሱረቱ አል ሙጃደላ – Al-Mujādalah
  59. ሱረቱ አል ሐሽር – Al-Hashr
  60. ሱረቱ አል ሙምተሂና – Al-Mumtahanah
  61. ሱረቱ አስ ሶፍ – As-Saff
  62. ሱረቱ አል ጁሙዓህ – Al-Jumu‘ah
  63. ሱረቱ አል ሙናፊቁን – Al-Munāfiqūn
  64. ሱረቱ አት ተጋቡን – At-Taghābun
  65. ሱረቱ አጥ ጠላቅ – At-Talāq
  66. ሱረቱ አት ተህሪም – At-Tahrīm
  67. ሱረቱ አል ሙልክ – Al-Mulk
  68. ሱረቱ አል ቀለም – Al-Qalam
  69. ሱረቱ አል ሓቃህ – Al-Hāqqah
  70. ሱረቱ አል መዓሪጅ – Al-Ma‘ārij
  71. ሱረቱ ኑህ – Nūh
  72. ሱረቱ አል ጂን – Al-Jinn
  73. ሱረቱ አል ሙዘሚል – Al-Muzzammil
  74. ሱረቱ አል ሙደሲር – Al-Muddaththir
  75. ሱረቱ አል ቂያማህ – Al-Qiyāmah
  76. ሱረቱ አል ኢንሳን – Al-Insān
  77. ሱረቱ አል ሙርሰላት – Al-Mursalāt
  78. ሱረቱ አን ነበእ – An-Naba’
  79. ሱረቱ አን ናዚዓት – An-Nāzi‘āt
  80. ሱረቱ ዐበሰ – ‘Abasa
  81. ሱረቱ አት ተክዊር – At-Takwīr
  82. ሱረቱ አል ኢንፊጣር – Al-Infitār
  83. ሱረቱ አል ሙጠፊፊን – Al-Mutaffifīn
  84. ሱረቱ አል ኢንሺቃቅ – Al-Inshiqāq
  85. ሱረቱ አል ቡሩጅ – Al-Burūj
  86. ሱረቱ አጥ ጣሪቅ – At-Tāriq
  87. ሱረቱ አል አዕላ – Al-A‘lā
  88. ሱረቱ አል ጋሺያህ – Al-Ghāshiyah
  89. ሱረቱ አል ፈጅር – Al-Fajr
  90. ሱረቱ አል በለድ – Al-Balad
  91. ሱረቱ አሽ ሸምስ – Ash-Shams
  92. ሱረቱ አል ለይል – Al-Layl
  93. ሱረቱ አድ ዱሓ – Ad-Duhā
  94. ሱረቱ አሽ ሸርህ – Ash-Sharh
  95. ሱረቱ አት ቲን – At-Teen
  96. ሱረቱ አል ዐለቅ – Al-‘Alaq
  97. ሱረቱ አል ቀድር – Al-Qadr
  98. ሱረቱ አል–በይናህ – Al-Bayyinah
  99. ሱረቱ አል ዘልዘላህ – Az-Zalzalah
  100. ሱረቱ አል ዓዲያት – Al-‘Ādiyāt
  101. ሱረቱ አል ቃሪዓሕ – Al-Qāri‘ah
  102. ሱረቱ አት ተካሱር – At-Takāthur
  103. ሱረቱ አል ዓስር – Al-‘Asr
  104. ሱረቱ አል ሁመዛህ – Al-Humazah
  105. ሱረቱ አል ፊል – Al-Feel
  106. ሱረቱ ቁረይሽ – Quraysh
  107. ሱረቱ አል ማዑን – Al-Mā‘ūn
  108. ሱረቱ አል ከውሰር – Al-Kawthar
  109. ሱረቱ አል ካፊሩን – Al-Kāfirūn
  110. ሱረቱ አን ነስር – An-Nasr
  111. ሱረቱ አል መሰድ – Al-Masad
  112. ሱረቱ አል ኢኽላስ – Al-Ikhlās
  113. ሱረቱ አል ፈለቅ – Al-Falaq
  114. ሱረቱ አን ናስ – An-Nās

አሰላሙ ዓለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ!
ይህ ዌየብሳይት ገና በመበልጸግ ላይ ያለ ስለሆነ ብዙ ስህተቶችን ልታገኙበት ትችላላችሁ። ስለዚህ እባካችሁ የምታገኟቸውን ስህተቶች በኮመንት ላይ እንዲታሳውቁን ስንል በአላህ ስም እንጠይቃለን።

Copyright © 2026 Amharic Quran.

Theme: Oceanly by ScriptsTown