Default Image
19, Dec 2023
86 – At-Taariq

86 – At-Taariq

(1) በሰማዩ በሌሊት መጪውም እምላለሁ፡፡(1) By the sky and the night comer –
(2) የሌሊት መጪውም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?(2) and how do you know what the night comer is?
(3) ጨለማን ቀዳጁ ኮከብ ነው፡፡(3) It is the star of piercing brightness –
(4) ነፍስ ሁሉ በእርሷ ላይ ጠባቂ ያለባት እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡(4) there is no soul except that there is a watcher over it.
(5) ሰውም ከምን እንደተፈጠረ ይመልከት፡፡(5) Let man reflect on what he was created from.
(6) ከተስፈንጣሪ ውሃ ተፈጠረ፡፡(6) He was created from a spurting fluid,
(7) ከጀርባና ከእርግብግብቶች መካከል የሚወጣ ከኾነ (ውሃ)፡፡(7) emerging from between the backbone and the ribs.
(8) እርሱ (አላህ) በመመለሱ ላይ በእርግጥ ቻይ ነው፡፡(8) Indeed, Allah is able to bring him back to life.
(9) ምስጢሮች በሚገለጡበት ቀን፡፡(9) On the Day when all secrets will be disclosed,
(10) ለእርሱም (ለሰው) ኀይልና ረዳት ምንም የለውም፡፡(10) he will then have no power, nor any helper.
(11) የመመለስ ባለቤት በኾነችው ሰማይም እምላለሁ፡፡(11) By the sky and its recurring rain,
(12) (በበቃይ) የመሰንጠቅ ባለቤት በኾነችው ምድርም፤(12) and by the earth that cracks open [with the sprout of plants],
(13) እርሱ (እውነትን ከውሸት) የሚለይ ቃል ነው፡፡(13) Indeed, this [Qur’an] is a decisive word,
(14) እርሱም ቀልድ አይደለም፡፡(14) which is not for amusement.
(15) እነርሱ በእርግጥ ተንኮልን ይሠራሉ፡፡(15) Indeed, they are devising a plan.
(16) (እኔ) ተንኮልንም እመልሳለሁ፡፡(16) I am too devising a plan.
(17) ከሓዲዎችንም ቀን ስጣቸው፡፡ ጥቂትን ጊዜ አቆያቸው፡፡(17) So bear with the disbelievers, and give them respite for a while.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

36 – Yaseen

36 – Yaseen (1) የ.ሰ.(ያ ሲን) (1) Yā Sīn (2) ጥበብ በተመላበት ቁርኣን እምላለሁ፡፡ (2) By the Qur’an, full of…

ሱረቱል አንዓም አማርኛ ቁርአን 6 Al anam Amharic Quran

ሱረቱል አንዓም አማርኛ ቁርአን 6 Al anam Amharic Quran الْحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ وَجَعَلَ الظُّلُمَاتِ وَالنُّورَ ۖ ثُمَّ الَّذِينَ…

95 – At-Tin

95 – At-Tin (1) በበለስና በዘይት ወይራ እምላለሁ፡፡ (1) By the fig and the olive [of Jerusalem], (2) በሲኒን ተራራም፤ (2)…