Default Image
10, Dec 2023
54 – Al-Qamar

54 – Al-Qamar

(1) ሰዓቲቱ (የትንሣኤ ቀን) ተቃረበች፤ ጨረቃም ተገመሰ፡፡(1) The Hour has drawn near and the moon has split asunder.
(2) ተዓምርንም ቢያዩ (ከእምነት) ይዞራሉ፡፡ (ይህ) «ዘውታሪ ድግምት ነውም» ይላሉ፡፡(2) Whenever they see a sign, they turn away and say, “Same old magic!”
(3) አስተባበሉም፡፡ ዝንባሌዎቻቸውንም ተከተሉ፡፡ ነገርም ሁሉ (ወሰን አለው)፤ ረጊ ነው፡፡(3) They deny [the truth] and follow their desires, but every matter will reach its inevitable end.
(4) ከዜናዎችም በእርሱ ውስጥ መገሰጥ ያለበት ነገር በእርግጥ መጣላቸው፡፡(4) There have already come to them stories [of destroyed nations] that are sufficient to deter them,
(5) ሙሉ የኾነች ጥበብ (መጣቻቸው) ግን አስፈራሪዎቹ አያብቃቁም፡፡(5) which contain extensive wisdom, but the warnings are of no avail.
(6) ከነርሱም ዙር፡፡ ጠሪው (መልአክ) ወደ አስደንጋጭ ነገር የሚጠራበትን ቀን (አስታውስ)፡፡(6) So turn away from them [O Prophet]. On the Day when the caller will summon them to a horrific event,
(7) ዓይኖቻቸው ያቀረቀሩ ኾነው፤ ፍጹም የተበተነ አንበጣ መስለው ከመቃብሮቹ ይወጣሉ፡፡(7) with eyes downcast, they will come out of the graves like scattered locusts,
(8) ወደ ጠሪው አንገቶቻቸውን ሳቢዎች ቸኳዮች ኾነው (ይወጣሉ)፡፡ ከሓዲዎቹ (ያን ጊዜ ምን ይላሉ?) «ይህ ብርቱ ቀን ነው» ይላሉ፡፡(8) rushing headlong towards the caller. The disbelievers will say, “This is a hard Day!”
(9) ከእነርሱ በፊት የኑሕ ነገድ አስተባበለች፡፡ ባሪያችንንም (ኑሕን) አስተባበሉ፡፡ «ዕብድ ነውም» አሉ፡፡ ተገላመጠም፡፡(9) The people of Noah rejected [the truth] before them; they rejected Our slave and said, “He is a madman,” and he was rebuked.
(10) ጌታውንም «እኔ የተሸነፍኩ ነኝና እርዳኝ» ሲል ጠራ፡፡(10) So he called upon his Lord, “I am overpowered, so help me!”
(11) ወዲያውም የሰማይን ደጃፎች በሚንቧቧ ውሃ ከፈትን፡፡(11) So We opened the gates of the sky with water pouring down in torrents,
(12) የምድርንም ምንጮች አፈነዳን፡፡ ውሃውም (የሰማዩና የምድሩ) በእርግጥ በተወሰነ ኹነታ ላይ ተገናኘ፡፡(12) and We caused the earth to burst forth with springs, then the waters met for a preordained purpose.
(13) ባለ ሳንቃዎችና ባለሚስማሮች በኾነችም ታንኳ ላይ ጫንነው፡፡(13) We carried him on an [Ark made] of planks and nails,
(14) በጥበቃችን ስር ኾና ትንሻለላለች፡፡ ተክዶ ለነበረው ሰው ምንዳ (ይህንን ሠራን)፡፡(14) sailing under Our [watchful] Eyes; as a reward for the one [they] denied.
(15) ተዓምር አድርገንም በእርግጥ ተውናት፡፡ ከተገሳጭም አልለን?(15) We have certainly left it as a sign; is there anyone to take heed?
(16) ቅጣቴና ማስጠንቀቂያዎቼም እንዴት ነበሩ?(16) Then how were My punishment and My warnings?
(17) ቁርኣንንም ለመገንዘብ በእርግጥ አገራነው፡፡ ተገንዛቢም አልለን?(17) We have certainly made the Qur’an easy to understand and remember; is there anyone to take heed?
(18) ዓድ አስተባበለች፡፡ ቅጣቴና ማስጠንቀቂያዎቼም እንዴት ነበሩ!(18) ‘Ād disbelieved. Then how were My punishment and My warnings?
(19) እኛ በእነርሱ ላይ ዘወትር መናጢ በኾነ ቀን በኀይል የምትንሻሻ ነፋስን ላክንባቸው፡፡(19) We sent against them a furious wind on a day of continuous misfortune,
(20) ሰዎቹን ልክ ከሥሮቻቸው የተጎለሰሱ የዘንባባ ግንዶች መስለው (ከተደበቁበት) ትነቅላቸዋለች፡፡(20) sweeping people away, as if they were trunks of uprooted palm trees.
(21) ቅጣቴና ማስጠንቀቂያዎቼም እንዴት ነበሩ?(21) Then how were My punishment and My warnings?
(22) ቁርኣንንም ለማስታወስ በእርግጥ አገራነው፡፡ ተገሳጭም አልለን?(22) We have certainly made the Qur’an easy to understand and remember; is there anyone to take heed?
(23) ሰሙድ በአስፈራሪዎቹ አስተባበለች፡፡(23) Thamūd rejected the warnings,
(24) «ከእኛ የኾነን አንድን ሰው እንከተለዋለን? እኛ ያን ጊዜ በስህተትና በዕብደት ውስጥ ነን» አሉ፡፡(24) They said, “Shall we follow a single human being from among us? Then we would surely be in error and insanity!
(25) «ከኛ መካከል በእርሱ ላይ (ብቻ) ማስገንዘቢያ (ራእይ) ተጣለለትን? አይደለም እርሱ ውሸታም ኩሩ ነው» (አሉ)፡፡(25) Has the revelation been sent down upon him out of all of us? Rather, he is an insolent liar.”
(26) ውሸታሙ ኩሩው ማን እንደኾነ ነገ በእርግጥ ያውቃሉ፡፡(26) Tomorrow they will know who the insolent liar is.
(27) እኛ ሴት ግመልን ለእነርሱ መፈተኛ ትኾን ዘንድ ላኪዎች ነን፡፡ ተጠባበቃቸውም፡፡ ታገስም፡፡(27) We are sending the she-camel as a test for them, so watch them [O Sālih] and be patient,
(28) ውሃውንም በመካከላቸው የተከፈለ መኾኑን ንገራቸው፡፡ ከውሃ የኾነ ፋንታ ሁሉ (ተረኞቹ) የሚጣዱት ነው፡፡(28) and tell them that the water is to be shared between them; each should take its drink in turn.
(29) ጓደኛቸውንም ጠሩ፡፡ ወዲያውም (ሰይፍን) ተቀበለ፡፡ ወጋትም፡፡(29) But they called their companion, and he undertook the task and hamstrung her.
(30) ቅጣቴና ማስጠንቀቂያዎቼም እንዴት ነበሩ?(30) Then how [terrible] My punishment and My warnings were!
(31) እኛ በእነርሱ ላይ አንዲትን ጩኸት ላክንባቸው፡፡ ወዲያውም ከበረት አጣሪ (አጥር) እንደ ተሰባበረ ርግጋፊ ኾኑ፡፡(31) We sent against them a single blast, leaving them like trampled hedge-building twigs.
(32) ቁርኣንንም ለመገንዘብ አገራነው፡፡ ተገሳጭም አልለን?(32) We have certainly made the Qur’an easy to understand and remember; is there anyone to take heed?
(33) የሉጥ ሕዝብ በአስፈራሪዎቹ አስተባበለች፡፡(33) The people of Lot rejected the warnings.
(34) እኛ በእነርሱ ላይ ጠጠርን ያዘለች ነፋስን ላክን፡፡ የሉጥ ቤተሰቦች ብቻ ሲቀሩ (እነርሱንስ) በሌሊት መጨረሻ ላይ አዳንናቸው፡፡(34) We sent against them a storm of pebbles, except the family of Lot whom We saved before dawn,
(35) ከእኛ በኾነ ጸጋ (አዳንናቸው)፡፡ እንደዚሁ ያመሰገነን ሰው እንመነዳለን፡፡(35) as a blessing from Us. Thus do We reward those who give thanks.
(36) ብርቱይቱን አያያዛችንንም በእርግጥ አስጠነቀቃቸው፡፡ በማስጠንቀቂያዎቹም ተከራከሩ፡፡(36) He had already warned them of Our punishing assault, but they doubted the warnings.
(37) ከእንግዶቹም እንዲያስመቻቸው ደጋግመው ፈለጉት፡፡ ወዲያውም ዓይኖቻቸውን አበስን፡፡ «ቅጣቴንና ማስጠንቀቂያዎቼንም ቅመሱ» (አልናቸው)፡፡(37) They even demanded that he let them have their way with his angel-guests, so We blinded their eyes, [saying], “Taste My punishment and My warnings!”
(38) በማለዳም ዘውታሪ የኾነ ቅጣት በእርግጥ ማለደባቸው፡፡(38) By the early morning a lasting torment overtook them.
(39) «ቅጣቴንና ማስጠንቀቂያዎቼንም ቅመሱ» (ተባሉ)፡፡(39) Taste My punishment and My warnings!
(40) ቁርኣንንም ለመገንዘብ በእርግጥ አገራነው፡፡ ተገሳጭም አልለን?(40) We have certainly made the Qur’an easy to understand and remember; is there anyone to take heed?
(41) የፈርዖንንም ቤተሰቦች ማስጠንቀቂያዎች በእርግጥ መጡዋቸው፡፡(41) Indeed, warnings came to the people of Pharaoh.
(42) በተዓምራቶቻችን በሁሏም አስተባበሉ፡፡ የብርቱ ቻይንም አያያዝ ያዝናቸው፡፡(42) But they rejected all of Our signs, so We seized them with the grip of the All-Mighty, Most Powerful.
(43) ከሓዲዎቻችሁ ከእነዚህ በላጮች ናቸውን? ወይስ ለናንተ በመጽሐፎች ውስጥ (የተነገረ) ነፃነት አላችሁን?(43) Are your disbelievers [O Makkans] superior than those, or have you been granted immunity in divine Scriptures?
(44) ወይስ «እኛ የተረዳን ክምቹዎች ነን» ይላሉን?(44) Or do they say, “We are a united front, bound to prevail.”?
(45) ክምቹዎቹ በእርግጥ ድል ይምመታሉ፡፡ ጀርባዎችንም ያዞራሉ፡፡(45) Soon their united front will be defeated, and they will flee.
(46) ይልቁንም ሰዓቲቱ (ትንሣኤ) ቀጠሮዋቸው ናት፡፡ ሰዓቲቱም በጣም የከበደችና የመረረች ናት፡፡(46) But the Hour is their appointed time, and the Hour is more catastrophic and more bitter.
(47) አመጸኞች በስህተትና በእሳቶች ውስጥ ናቸው፡፡(47) Indeed, the wicked are in error and will be in blazes.
(48) በእሳት ውስጥ በፊቶቻቸው በሚጎተቱበት ቀን «የሰቀርን መንካት ቅመሱ» (ይባላሉ)፡፡(48) On the Day when they will be dragged into the Fire on their faces, [they will be told], “Taste the agony of Hell!”
(49) እኛ ሁሉን ነገር በልክ ፈጠርነው፡፡(49) Indeed, We have created everything according to a determined measure.
(50) ትእዛዛችንም እንደ ዓይን ቅጽበት አንዲት (ቃል) እንጅ ሌላ አይደለም፡፡(50) Our command is but a single word, which is fulfilled in the blink of an eye.
(51) ብጤዎቻችሁንም በእርግጥ አጠፋን፡፡ ተገሳጭም አልለን?(51) We have destroyed many like you [O Makkans]; is there anyone to take heed?
(52) የሠሩትም ነገር ሁሉ በመጽሐፎች ውስጥ ነው፡፡(52) Everything they did is in the written records,
(53) ትንሹም ትልቁም ሁሉ የተጻፈ ነው፡፡(53) and everything, small or big, is written down.
(54) አላህን ፈሪዎቹ በአትክልቶችና በወንዞች ውስጥ ናቸው፡፡(54) Indeed, the righteous will be in gardens and rivers,
(55) (እነርሱም ውድቅ ቃልና መውወንጀል በሌለበት) በእውነት መቀመጫ ውስጥ ቻይ የሆነው ንጉሥ ዘንድ ናቸው፡፡(55) seated in honor in the presence of the Most Powerful Sovereign.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

88 – Al-Ghaashiya

88 – Al-Ghaashiya (1) የሸፋኝቱ (ትንሣኤ) ወሬ መጣህን? (1) Has there come to you the story of the Overwhelming Event? (2) ፊቶች…

61 – As-Saff

61 – As-Saff (1) በሰማያት ውስጥ ያለው በምድርም ውስጥ ያለው ሁሉ ለአላህ አሞገሠ፡፡ እርሱም አሸናፊው ጥበበኛው ነው፡፡ (1) All that…

90 – Al-Balad

90 – Al-Balad (1) በዚህ አገር (በመካ) እምላለሁ፡፡ (1) I do swear by this city [of Makkah] – (2) አንተ በዚህ አገር ሰፋሪ ስትኾን፡፡…