Default Image
11, Dec 2023
68 – Al-Qalam

68 – Al-Qalam

(1) ነ.(ኑን)፤ በብርእ እምላለሁ በዚያም (መልአኮች) በሚጽፉት፡፡(1) Nūn. By the pen and what they [the angels] write [in the Records of men],
(2) አንተ በጌታህ ጸጋ የተጎናጸፍክ ስትኾን ዕብድ አይደለህም፡፡(2) By the grace of your Lord [O Prophet], you are not a madman.
(3) ላንተም (ከጌታህ) የማይቋረጥ ዋጋ በእርግጥ አልለህ፡፡(3) You will surely have a never-ending reward.
(4) አንተም በታላቅ ጠባይ ላይ ነህ፡፡(4) Indeed, you are of a great moral character.
(5) ወደፊትም ታያለህ፤ ያያሉም፡፡(5) Soon you will see and they will see,
(6) ዕብደት በማንኛችሁ እንዳልለ፡፡(6) which of you is afflicted with madness.
(7) ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም ተመሪዎቹን ዐዋቂ ነው፡፡(7) Indeed, your Lord alone knows best who has strayed from His way and those who are rightly guided.
(8) ለአስተባባዮችም አትታዝዙ፡፡(8) So do not obey the deniers.
(9) ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡(9) They wish that you would compromise so they would too compromise.
(10) ወራዳንም ሁሉ አትታዘዝ፡፡(10) And do not obey every disgraceful swearer,
(11) ሰውን አነዋሪንና በማሳበቅ ኼያጅን፡፡(11) backbiter, gossip-monger,
(12) ለበጎ ነገር በጣም ከልካይን፣ ወሰን አላፊን፣ ኃጢአተኛን፤(12) withholder of good, transgressor, sinful,
(13) ልበ ደረቅን፣ ከዚህ በኋላ ዲቃላን (ሁሉ አትታዘዝ)፡፡(13) coarse, and furthermore, an illegitimate child.
(14) የገንዘብና የልጆች ባለቤት በመኾኑ (ያስተባብላል)፡፡(14) Simply because he has wealth and children,
(15) በእርሱ ላይ አንቀጾቻችን በሚነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡(15) When Our verses are recited to him, he says, “Ancient fables!”
(16) በአፍንጫው ላይ በእርግጥ (የሚነወርበት) ምልክት እናደርግበታለን፡፡(16) We will soon brand him on the snout.
(17) እኛ የአትክልቲቱን ባለቤቶቸ እንደ ሞከርን (የመካን ሰዎች) ሞከርናቸው፡፡ ማልደው (ፍሬዋን) ሊለቅሟት በማሉ ጊዜ፡፡(17) Indeed, We have tested them [the Makkans] as We tested the people of the garden, when they swore to harvest its fruits in the early morning,
(18) (በመሓላቸው) አያስቀሩምም፡፡(18) and made no exception [by saying: if Allah wills].
(19) እነርሱ የተኙ ኾነውም ሳሉ ከጌታህ የኾነ ዟሪ በእርሷ ላይ ዞረባት፡፡(19) Then it was struck by an affliction from your Lord while they were asleep,
(20) እንደ ሌሊት ጨለማም ኾና አነጋች፤ (ከሰለች)፡፡(20) and it turned to ashes as black as night.
(21) ያነጉም ኾነው ተጠራሩ፡፡(21) Then in the early morning they called out to one another:
(22) «ቆራጮች እንደ ኾናችሁ በእርሻቸሁ ላይ ማልዱ» በማለት፡፡(22) “Go early to your garden if you really wish to harvest.”
(23) እነርሱ የሚንሾካሾኩ ኾነው ኼዱም፡፡(23) So they set out, whispering to one another,
(24) ዛሬ በእናንተ ላይ ድኻ እንዳይገባት በማለት፡፡(24) “Not a single poor person should enter your garden today.”
(25) (ድኾችን) በመከልከልም ላይ (በሐሳባቸው) ቻዮች ኾነው ማለዱ፡፡(25) And they left early, fully determined to stick to their plan.
(26) (ተቃጥላ) ባዩዋትም ጊዜ «እኛ በእርግጥ ተሳሳቾች ነን» አሉ፡፡(26) But when they saw the garden, they said, “We must have lost our way!
(27) «ይልቁንም እኛ የተከለከልን ነን» አሉ፡፡(27) Rather, we have been deprived.”
(28) ትክክለኛቸው «ለእናንተ አላህን ለምን አታጠሩም አላልኳችሁምን?» አላቸው፡፡(28) The best among them said, “Did I not say to you to glorify Allah?”
(29) «ጌታችን ጥራት ይገባው፡፡ እኛ በዳዮች ነበርን፤» አሉ፡፡(29) They said, “Glory be to our Lord! We were truly wrongdoers.”
(30) የሚወቃቀሱም ኾነው ከፊሎቻቸው በከፊሉ ላይ መጡ፡፡(30) Then they turned to one another, throwing blame.
(31) «ዋ ጥፋታችን! እኛ ድንበር አላፊዎች ነበርን፤» አሉ፡፡(31) They said, “Woe to us! We were surely transgressors.
(32) «ጌታችን ከእርሷ የተሻለን (አትክልት) ሊለውጠን ይከጀላል፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ከጃዮች ነን፤» (አሉ)፡፡(32) Our Lord may give us something better than this. We certainly turn to our Lord in hope.”
(33) ቅጣቱ እንደዚሁ ነው፡፡ የመጨረሻይቱም ዓለም ቅጣት ታላቅ ነው፡፡ የሚያውቁት በኾኑ ኖሮ (በተጠነቀቁ ነበር)፡፡(33) Such is the punishment [in this world]; but the punishment of the Hereafter is far worse, if only they knew.
(34) ለጥንቁቆቹ በጌታቸው ዘንድ መጠቀሚያ ገነቶች አሏቸው፡፡(34) Indeed, the righteous will have gardens of bliss with their Lord.
(35) ሙስሊሞቹን እንደ ከሓዲዎች እናደርጋለን?(35) Should We then treat Muslims like the wicked?
(36) ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ፡፡(36) What is the matter with you that you make such a judgment?
(37) በእውነቱ ለእናንተ በእርሱ የምታጠኑበት መጽሐፍ አላችሁን?(37) Or do you have a scripture in which you read
(38) በውስጡ ለእናንተ የምትመርጡት አላችሁ (የሚል)(38) that you will be given whatever you choose?
(39) ወይስ ለእናንተ የምትፈርዱት አላችሁ በማለት (ቃል ኪዳን የገባንላችሁ) እስከ ትንሣኤ ቀን ደራሽ የኾኑ መሓላዎች ለእናንተ በእኛ ላይ አሏችሁን?(39) Or do you have a solemn promise binding upon Us until the Day of Resurrection, that you will have whatever you decide for yourselves?
(40) በዚህ ማንኛቸው ተያያዥ እንደ ኾነ ጠይቃቸው፡፡(40) Ask them which of them can guarantee that.
(41) ወይስ ለእነርሱ (በፍርዳቸው ተስማሚ) «ተጋሪዎች» አሏቸውን? እውነተኞችም እንደኾኑ «ተጋሪዎቻቸውን» ያምጡ፡፡(41) Or do they have associate-gods? Then let them bring forth their associate-gods, if they are truthful.
(42) ባት የሚገለጥበትን (ከሓዲዎች) ወደ መስገድም የሚጥጠሩበትንና የማይችሉበት ቀን (አስታውስ)፡፡(42) On the Day when the Shin [of Allah] will be uncovered, and they are invited to prostrate, but they will not be able to do so.
(43) ዓይኖቻቸው የፈሩ ውርደት የምትሸፍናቸው ሲኾኑ፤ (ወደ ስግደት የሚጠሩበትን)፤ እነርሱም (በምድረ ዓለም) ደህና ኾነው ሳሉ ወደ ስግደት በእርግጥ ይጠሩ ነበሩ፡፡(43) Their eyes will be downcast, overwhelmed with humiliation, for they were invited to prostrate when they were capable [but they refused].
(44) በዚህም ንግግር ከሚያስተባብሉት ሰዎች ጋር ተዎኝ፡፡ (እነርሱን እኔ እበቃሃለሁ)፡፡ ከማያውቁት ስፍራ አዘናግተን እንይዛቸዋለን፡፡(44) So leave to Me those who reject this message [O Prophet]. We will gradually lead them to their ruin in ways that they do not perceive.
(45) እነርሱንም አዘገያለሁ፡፡ ዘዴዬ ብርቱ ነውና፡፡(45) I will give them respite, but My plan is firm.
(46) በእውነቱ ዋጋን ትጠይቃቸዋለህን? ስለዚህ እነርሱ ከዕዳ የተከበዱ ናቸውን?(46) Or are you asking them for a reward, so they find it too burdensome?
(47) ወይስ እነርሱ ዘንድ የሩቁ ምስጢር ዕውቀት አልለን? ስለዚህ እነርሱ ይጽፋሉን?(47) Or do they have knowledge of the unseen, so they write it down?
(48) ለጌታህም ፍርድ ታገሥ፤ (በመበሳጨትና ባለ መታገሥ) እንደ ዓሣው ባለቤትም (እንደ ዮናስ) አትኹን፡፡ እርሱ በጭንቀት የተመላ ኾኖ (ጌታውን) በተጣራ ጊዜ፡፡(48) So be patient with the decree of your Lord, and do not be like [Jonah], the man of the Whale, when he cried out in anguish.
(49) ከጌታው የኾነ ጸጋ ባላገኘው ኖሮ በምድረ በዳ ተወቃሽ ኾኖ በተጣለ ነበር፡፡(49) Had it not been for the grace that he received from his Lord, he would have surely been thrown onto the barren shore, blameworthy.
(50) ጌታውም (በነቢይነት) መረጠው፡፡ ከደጋጎቹም አደረገው፡፡(50) But his Lord chose him, and made him one of the righteous.
(51) እነሆ እነዚያም የካዱት ሰዎች ቁርኣኑን በሰሙ ጊዜ በዓይኖቻቸው ሊጥሉህ (ሊያጠፉህ) ይቀርባሉ፡፡ «እርሱም በእርግጥ ዕብድ ነው» ይላሉ፡፡(51) The disbelievers would almost strike you down with their malicious gazes when they hear the Reminder, and they say, “He is certainly mad.”
(52) ግን እርሱ (ቁርኣን) ለዓለማት መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም፡፡(52) But it is nothing other than a reminder to the whole world.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

ሱረቱ አል ሒጅር አማርኛ ቁርአን // Free Amharic Quran Suretu Al-Hijr

ሱረቱ አል ሒጅር አማርኛ ቁርአን // Free Amharic Quran Suretu Al-Hijr الر ۚ تِلْكَ آيَاتُ الْكِتَابِ وَقُرْآنٍ مُّبِينٍ  [1] (1)…

67 – Al-Mulk

67 – Al-Mulk (1) ያ ንግሥና በእጁ የኾነው አምላክ ችሮታው በዛ፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው፡፡ (1) Blessed is…

70 – Al-Ma’aarij

70 – Al-Ma’aarij (1) ወዳቂ ከኾነው ቅጣት ጠያቂ ጠየቀ፡፡ (1) A challenger asked for a punishment bound to come (2)…