Skip to content

Amharic Quran

ከመሞትህ በፊት ቁርአንን አንብብ! (Read the holy Quran before you die!)

  • Amharic Quran
    • ድጋፍ ያድርጉልን
  • Blog
    • ቁርአንን እንረዳው
    • Quran in Oromigna

አል-ፋቲሐ (ቅዱስ ቁርአን ፣ ምዕራፍ 1) ቁርአን በአማርኛ ቋንቋ

Posted on November 19, 2023April 9, 2026 By Amharic Quran 7 Comments on አል-ፋቲሐ (ቅዱስ ቁርአን ፣ ምዕራፍ 1) ቁርአን በአማርኛ ቋንቋ
ቁርአንን እንረዳው

አል-ፋቲሐህ (ቅዱስ ቁርአን ፣ ምዕራፍ 1)

بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ  [1] «ቢስሚላሂ አር-ረሕማኒ አር-ረሒሂም»
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው (እጀምራለሁ)።
In the name of Allah, the Most Compassionate, the Most Merciful.

ኢብኑ ዐባስ እንደዘገቡት፦ ነብዩ የአንድን ምዕራፍ
ማብቃት ያውቁት የነበረው «ቢስሚላሂ አር-ረሕማኒ አር-ረሒሂም» ሲወርድ ነበር» ብለዋል።

አቡዳውድ እንደዘገቡትም፣ ዐብዱላህ ብን መስዑድ፦ «በሁለት ምዕራፎች መካከል መለያ ማወቅ
የጀመርነው «ቢስሚላ አር-ረሕማኒ አር-ረሂሒም» ከወረደ ወዲህ ነው» ብለዋል። ዐብዱላህ ብን
ዑመር፦ «ቢስሚላሂ አር-ረሕማኒ አር-ረሒሂም» ከሁሉም ምዕራፍ ጋር አብሮ ወርዷል» ብለዋል።
(ዋሒዲ እና ሱዩጢ)

الْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ  [2]

ምስጋና ለአላህ ይገባው የዓለማት ጌታ ለኾነው፤ (All praise be to Allah, the Lord of the worlds,)

الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ  [3]

እጅግ በጣም ርኅሩህ በጣም አዛኝ (the Most Compassionate, the Most Merciful,)

مَالِكِ يَوْمِ الدِّينِ  [4]

የፍርዱ ቀን ባለቤት ለኾነው፡፡ (Master of the Day of Judgment.)

إِيَّاكَ نَعْبُدُ وَإِيَّاكَ نَسْتَعِينُ  [5]

አንተን ብቻ እንግገዛለን፤ አንተንም ብቻ እርዳታን እንለምናለን፡፡ (You alone we worship, and You alone we ask for help.)

اهْدِنَا الصِّرَاطَ الْمُسْتَقِيمَ  [6]

ቀጥተኛውን መንገድ ምራን፡፡ (Guide us to the straight path,)

صِرَاطَ الَّذِينَ أَنْعَمْتَ عَلَيْهِمْ غَيْرِ الْمَغْضُوبِ عَلَيْهِمْ وَلَا الضَّالِّينَ  [7]

የእነዚያን በነርሱ ላይ በጎ የዋልክላቸውን በነሱ ላይ ያልተቆጣህባቸውንና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ (ምራን፤ በሉ)፡፡ (the path of those whom You have blessed; not of those who incurred Your Wrath, or of those who went astray.)

በዚህ ምዕራፍ መጨረሻ ላይ ኣሚን (ዱዓችንን ተቀበለን) የሚለዉን ቃል ማንበብ ተገቢ ነው። አህመድና ኢብኑ ማጃህ በዘገቡት ሐዲስ ነብዩ (صلى الله عليه وسلم(፦ «አይሁዶች በሰላታችሁና ኣሚን በማለታችሁ የተመቀኟችሁን ያህል በምንም ነገር አልተመቀኟችሁም» ብለዋል። ትርጉሙም ዱዓችንን ተቀበለን ማለት ነው። ኢማምም የሆነ ሰው ቢሆን በትክከለኛው አባባል ፋቲሃን አንብቦ ሲያበቃ ድምፁን ከፍ አድርጎ ማንበብ ተገቢ መሆኑን ዋኢል ብን ሁጅር የተባሉት ሱሃቢ ነቢዩ ሙሐመድ (صلى الله عليه وسلم (ወለዷሊን) የሚለዉን ካነበቡ በኋላ ድምፃቸዉን ከፍ አድርገው ኣሚን የሚለዉን ሳብ በማድረግ ያነቡት ነበር ብለዋል። ብቻዉን ሰጋጅና ተከታይ የሆነ ሰው በሁሉም ዘንድ ማለቱ ተገቢ ነው።

ከመክፈቻው ምዕራፍ ከምናገኛቸው ዋና ዋና ነጥቦች መካከል በጥቂቱ:-

  1. ምስጋና በሙሉ የሚገባው የሁለንተናዊው ዓለም ፈጣሪና ተንከባካቢ ለሆነው ለአላህ ብቻ
    እንደሆነ፤
  2. አላህ የሰው ልጆች በምድራዊ ቆይታቸው በሰሩት ስራ ምንዳ በሚያገኙበት የትንሳኤ ቀን ብቸኛ
    ፍርድ ሰጪ ጌታ መሆኑን፤
  3. ከዱዓ ስርዓቶች መካከል ቅድሚያ አላህን ማሞገስ አስፈላጊ መሆኑን፤
  4. ለምድራዊም ሆነ አኼራዊ ጉዳዩች ብቸኛው ተለማኝ አንድ አላህ ብቻና ብቻ እንደሆነ፤ ከርሱም
    በስተቀር ሊመለክና እርዳታ ሊጠየቅ የሚችል ሌላ አካል እንደሌለና በፍፁምነት ለእሱ
    መተናነስና እርሱን ብቻ መጠየቅ እንደሚገባ፤
  5. አላህ መልካም ስሞችና ንፁህ ባህሪያት እንዳሉት እና ከባህሪያቶቹም እጅግ በጣም አዛኝና
    ሩህሩህ የሚሉት ስሞች ግንባር ቀደም መሆናቸውን፤
  6. ቀጥተኛው መንገድ የሚባለው የነብያትን ፈለግ የተከተሉ ሁሉ የተጓዙበት በመሆኑንና የእነርሱን አርአያነት
    መከተል ከምንም በላይ አስፈላጊ መሆኑን፤
  7. የአላህ ቁጣ ያደረባቸውን ሰዎች መንገድ ከመከተል መታቀብ ግዴታ መሆኑንና ለዚህም የአላህ
    እገዛ አስፈላጊ እንደሆነና ሁሌም ቀጥተኛውን መንገድ ይመራን ዘንድ የእሱን እገዛ መጠየቅ እንዳለብን፤
  8. ወደ ቅኑዉም ሆነ መጥፎው መምራት የአላህ ስልጣን በመሆኑ ወደ ቅኑዉ እንዲመራን እሱን
    ብቻ መማፀን እንዳለብን፤
  9. ከአላህ ሌላ ያለን አካል ነብያትንም ሆነ ወሊዮችን እርዳታ መጠየቅ ተገቢ አለመሆኑን
    እንማራለን።

ሰዎች የእለት ጉርሳቸውን ይለምናሉ። እኛ ግን ዘላለማዊ ምሪትን እንለምናለን። ሰውየው ሙስሊምም ቢሆን በየጊዜው ሊሳሳት፣ የተሳሳተ ውሳኔ ሊወስን፣ ሰዎችን ሊበድል፣ ብሎም ከኢስላም ሊወጣ ይችላል፣ ስለዚህ የአላህን ምሪት አጥብቆ መለመን እጅግ በጣም አንገብጋቢ ጉዳይ ነው።

Tags: suret al fatiha in Amharic Arabic English and phonetics አል-ፋቲሐ (ቅዱስ ቁርአን ፣ ምዕራፍ 1) ቁርአን በአማርኛ ቋንቋ

Post navigation

❮ Previous Post: ይህን የአማርኛ ቁርአን ዳውንሎድ ማንበብ ይችላሉ
Next Post: ሱረቱል አል-በቀራህ አማርኛ ቅዱስ ቁርአን ምዕራፍ 2 Amharic Quran ❯

7 thoughts on “አል-ፋቲሐ (ቅዱስ ቁርአን ፣ ምዕራፍ 1) ቁርአን በአማርኛ ቋንቋ”

  1. Biniyam Abera says:
    August 18, 2025 at 11:33 pm

    አሰላም ዓለይኩም ቁርአን በአማርኛ እፈልጋለሁ።

    Reply
    1. Muhammed says:
      December 2, 2025 at 4:10 pm

      ሙሉውን የአማርኛቁርአን ከነማብራሪያው እዚህ ያገኙታል። https://amharicquran.com/download/complete-quran-in-amharic-pdf-read-the-holy-quran-tafsir-in-the-amharic-language/

      Reply
    2. Zahra Omer says:
      June 9, 2026 at 10:04 am

      💖💖💖💖

      Reply
  2. Biniyam Abera says:
    August 18, 2025 at 11:34 pm

    ሁሉንም 30 ጁዝ ቁረዐን በአማርኛ ማግኘት ፈልጌ ነበር።

    Reply
    1. Muhammed says:
      December 2, 2025 at 4:10 pm

      ሙሉውን የአማርኛቁርአን ከነማብራሪያው እዚህ ያገኙታል። https://amharicquran.com/download/complete-quran-in-amharic-pdf-read-the-holy-quran-tafsir-in-the-amharic-language/

      Reply
    2. Ahmed Abdela says:
      April 26, 2026 at 6:31 pm

      ሁሉንም 30 ጁዝ ቁረዐን በአማርኛ ማግኘት ፈልጌ ነበር።

      Reply
      1. Muhammed says:
        July 7, 2026 at 9:21 am

        ሙሉውን የአማርኛቁርአን ከነማብራሪያው እዚህ ያገኙታል። https://amharicquran.com/download/complete-quran-in-amharic-pdf-read-the-holy-quran-tafsir-in-the-amharic-language/

        Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

  • Amharic Quran
  • Blog
  • Amharic Quran
  • Blog

Copyright © 2026 Amharic Quran.

Theme: Oceanly Green by ScriptsTown