Default Image
17, Dec 2023
81 – At-Takwir

81 – At-Takwir

(1) ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤(1) When the sun is wrapped up in darkness,
(2) ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤(2) and when the stars are scattered,
(3) ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤(3) and when the mountains are vanished,
(4) የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤(4) and when pregnant camels are left unattended,
(5) እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤(5) and when wild beasts are gathered,
(6) ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤(6) and when the seas are set on fire,
(7) ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤(7) and when the souls are sorted,
(8) በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤(8) and when the baby girl buried alive is asked,
(9) በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤(9) for what crime she was killed,
(10) ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤(10) and when records of deeds are spread open,
(11) ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤(11) and when the sky is stripped away,
(12) ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤(12) and when the Blazing Fire is flared up,
(13) ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤(13) and when Paradise is brought near –
(14) ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤(14) then every soul will know what it has brought about.
(15) ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡(15) I swear by the receding stars,
(16) ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡(16) that rise and hide,
(17) በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤(17) and by the night as it departs,
(18) በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡(18) and by the day as it breaks –
(19) እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡(19) Indeed, this [Qur’an] is a word conveyed by a noble angel-messenger.
(20) የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡(20) extremely powerful, highly revered with the Lord of the Throne,
(21) በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡(21) obeyed [by other angels] and moreover, trustworthy.
(22) ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡(22) Your fellow [the Prophet] is not madman.
(23) በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡(23) He indeed saw him [Gabriel] on the clear horizon.
(24) እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡(24) He does not withhold [knowledge of] the unseen.
(25) እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡(25) This [Qur’an] is not the word of an accursed devil.
(26) ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?(26) So which way are you going?
(27) እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡(27) It is but a reminder to the worlds,
(28) ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡(28) for those among you who wish to take the straight path.
(29) የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡(29) But you cannot wish except by the Will of Allah, the Lord of the worlds.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

112 – Al-Ikhlaas

112 – Al-Ikhlaas (1) በል «እርሱ አላህ አንድ ነው፡፡ (1) Say: He is Allah, the One; (2) «አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው፡፡ (2)…

ሱረቱል አል ዒምራን አማርኛ ቁርአን / Al-Imraan

ሱረቱል አል ዒምራን አማርኛ ቁርአን / Al-Imraan الم [1] Alif-Laam-Meeem (1) አ.ለ.መ (አሊፍ ላም ሚም)፤ (1) Alif Lām Mīm. اللَّهُ…

55 – Ar-Rahmaan

55 – Ar-Rahmaan (1) አል-ረሕማን፤ (1) The Most Compassionate, (2) ቁርኣንን አስተማረ፡፡ (2) has taught the Qur’an, (3) ሰውን ፈጠረ፡፡…