Default Image
19, Dec 2023
89 – Al-Fajr

89 – Al-Fajr

(1) በጎህ እምላለሁ፡፡ (1) By the dawn,
(2) በዐሥር ሌሊቶችም፡፡ (2) and the ten nights,
(3) በጥንዱም በነጠላውም፡፡ (3) and the even and the odd,
(4) በሌሊቱም በሚኼድ ጊዜ፡፡ (4) and by the night when it comes,
(5) በዚህ (መሓላ) ለባለ አእምሮ ታላቅ መሓላ አለበትን? (5) are these oaths not sufficient for those who have sense?
(6) ጌታህ በዓድ እንዴት እንደ ሠራ አታውቅምን? (6) Have you not considered how your Lord dealt with ‘Ād
(7) በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡ (7) of Iram, who were people of great stature,
(8) በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡ (8) the like of whom had never been created in the land;
(9) በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡ (9) and Thamūd, who carved out the rocks in the Valley;
(10) በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡ (10) and the mighty and powerful Pharaoh?
(11) በእነዚያ በአገሮች ላይ ግፍ የሠሩ፡፡ (11) All of them transgressed in the land,
(12) በእርሷም ውስጥ ጥፋትን ያበዙ በኾኑት (እንዴት እንደሠራ አታውቅምን?) (12) and spread therein much corruption,
(13) በእነርሱ ላይም ጌታህ የቅጣትን አለንጋ አወረደባቸው፡፡ (13) so your Lord poured upon them a scourge of punishment.
(14) ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና፡፡ (14) Indeed, your Lord is ever vigilant.
(15) ሰውማ ጌታው በሞከረው ጊዜ፣ ባከበረውና ባጣቀመውም (ጊዜ) «ጌታዬ አከበረኝ (አበለጠኝ)» ይላል፡፡ (15) As for man, when he is tested by his Lord by honoring him and bestowing blessings upon him, he says, “My Lord has [deservedly] honored me!”
(16) በሞከረውና በእርሱ ላይ ሲሳዩን ባጠበበ ጊዜማ «ጌታዬ አሳነሰኝ» ይላል፡፡ (16) But when he is tested by restricting his provision, he says, “My Lord has [undeservedly] humiliated me!”
(17) ይከልከል፤ ይልቁንም የቲምን አታከብሩም፡፡ (17) No indeed! You are not kind to the orphan,
(18) ድኻንም በማብላት ላይ አትታዘዙም፡፡ (18) nor do you urge one another to feed the needy,
(19) የውርስንም ገንዘብ የመሰብሰብን አበላል ትበላላችሁ፡፡ (19) and you greedily consume the entire inheritance,
(20) ገንዘብንም ብዙን መውደድ ትወዳላችሁ፡፡ (20) and love wealth immensely.
(21) ተዉ፤ ምድር ደጋግማ በተሰባበረች ጊዜ፤ (21) No indeed! When the earth is crushed over and over,
(22) መላእክትም ሰልፍ ሰልፍ ኾነው ጌታህ (ለሱ ክብር በምስማማ መልኩ) በመጣ ጊዜ፤ (22) and your Lord comes with the angels, rank after rank,
(23) ገሀነምም በዚያ ቀን በተመጣች ጊዜ በዚያ ቀን ሰው (ጥፋቱን) ይገነዘባል፡፡ መገንዘብም ለእርሱ ከየቱ? (23) and Hell is brought near on that Day – this is when man will understand, but what is the use of that understanding?
(24) «ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡ (24) He will say, “Would that I had sent forth something for my [eternal] life!”
(25) በዚያ ቀንም የርሱን አቀጣጥ አንድም አይቀጣም፡፡ (25) None can punish as He punishes on that Day,
(26) የእርሱንም አስተሳሰር አንድም አያስርም፡፡ (26) and none can bind as He binds.
(27) (ለአመነች ነፍስም) «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ! (27) [It will be said to the believer,] “O the tranquil soul!
(28) «ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡ (28) Return to your Lord, well pleased and pleasing [to Him].
(29) «በባሮቼም ውስጥ ግቢ፡፡ (29) Join My [righteous] slaves,
(30) ገነቴንም ግቢ፤» (ትባላለች)፡፡ (30) and enter My Paradise.”

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

ግደሉ የሚለው ቁርአን ወይስ መፅሀፍ ቅዱስ?

ግደሉ የሚለው ቁርአን ወይስ መፅሀፍ ቅዱስ? የግድያ መፅሀፍ የሚመስለው ቅዱስ ቁርአን ወይስ መፅሀፍ ቅዱስ? እስኪ ከመፅሀፍ ቅዱስ ጀምረን እንየው:- ግደል…

87 – Al-A’laa

87 – Al-A’laa (1) ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡ (1) Glorify the name of your Lord, the Most High,…

27 – An-Naml

27 – An-Naml (1) ጠ.ሰ (ጣ ሲን) ይህቺ ከቁርኣኑና ከገላጩ መጽሐፍ አንቀጾች ናት፡፡ (1) Tā Sīn. These are the verses of the…