Default Image
19, Dec 2023
92 – Al-Lail

92 – Al-Lail

(1) በሌሊቱ እምላለሁ (በጨለማው) በሚሸፍን ጊዜ፡፡ (1) By the night when it covers,
(2) በቀኑም፤ በተገለጸ ጊዜ፡፡ (2) and by the day when it appears,
(3) ወንድንና ሴትን በፈጠረውም (አምላክ እምላለሁ)፡፡ (3) and by His creation of male and female,
(4) ሥራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው፡፡ (4) surely your efforts are divergent.
(5) የሰጠ ሰውማ ጌታውን የፈራም፡፡ (5) As for the one who gives in charity and fears Allah,
(6) በመልካሚቱም (እምነት) ያረጋገጠ፤ (6) and truly believes in the best reward,
(7) ለገሪቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡ (7) We will make easy for him the way of salvation.
(8) የሰሰተ ሰውማ የተብቃቃም፤ (በራሱ የተመካ)፤ (8) But as for the one who is miserly and deems himself self-sufficient,
(9) በመልካሚቱ (እምነት) ያሰተባበለም፤ (9) and denies the best reward,
(10) ለክፉይቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡ (10) We will make easy for him the way of perdition.
(11) በወደቀም ጊዜ ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመውም፡፡ (11) His wealth will be of no avail to him when he tumbles [into Hell].
(12) ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን፡፡ (12) Indeed, it is upon Us to show the right way,
(13) መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛ ናቸው፡፡ (13) and surely to Us belong the Hereafter and the present life.
(14) የምትንቀለቀልንም እሳት አስጠነቀቅኳችሁ (በላቸው)፡፡ (14) So I warn you of a raging Fire,
(15) ከጠማማ በቀር ሌላ የማይገባት የኾነችን፡፡ (15) none will enter it except the most wretched,
(16) ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝ የሸሸው፡፡ (16) who denied and turned away.
(17) አላህን በጣም ፈሪውም በእርግጥ ይርቃታል፡፡ (17) But the most righteous will be saved from it,
(18) ያ የሚጥራራ ኾኖ ገንዘቡን (ለድኾች) የሚሰጠው፡፡ (18) who spends his wealth to purify himself,
(19) ለአንድም ሰው እርሱ ዘንድ የምትመለስ ውለታ የለችም፡፡ (19) not in return for someone’s favors,
(20) ግን የታላቅ ጌታውን ውዴታ ለመፈለግ (ይህንን ሠራ)፡፡ (20) but to seek the pleasure of his Lord, the Most High.
(21) ወደፊትም በእርግጥ ይደሰታል፡፡ (21) He will surely be well pleased.

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

63 – Al-Munaafiqoon

63 – Al-Munaafiqoon (1) መናፍቃን በመጡህ ጊዜ «አንተ የአላህ መልክተኛ መኾንህን በእርግጥ (ምለን) እንመሰክራለን» ይላሉ፡፡ አላህም አንተ በእርግጥ መልክተኛው መኾንህን ያውቃል፡፡ አላህም…

38 – Saad

38 – Saad (1) ጸ. (ሷድ) የክብር ባለቤት በሆነው ቁርኣን እምላለሁ (ብዙ አማልክት አሉ እንደሚሉት አይደለም)፡፡ (1) Sād. By the Qur’an, full of…

ሱረቱ አል አንፋል አማርኛ ቁርአን Free Amharic Quran 8 Al-Anfaal

ሱረቱ አል አንፋል አማርኛ ቁርአን Free Amharic Quran 8 Al-Anfaal يَسْأَلُونَكَ عَنِ الْأَنفَالِ ۖ قُلِ الْأَنفَالُ لِلَّهِ وَالرَّسُولِ ۖ فَاتَّقُوا…