Default Image
11, Dec 2023
63 – Al-Munaafiqoon

63 – Al-Munaafiqoon

(1) መናፍቃን በመጡህ ጊዜ «አንተ የአላህ መልክተኛ መኾንህን በእርግጥ (ምለን) እንመሰክራለን» ይላሉ፡፡ አላህም አንተ በእርግጥ መልክተኛው መኾንህን ያውቃል፡፡ አላህም መናፍቃን (ከልብ እንመሰክራለን በማለታቸው) ውሸታሞች መኾናቸውን ይመሰክራል፡፡(1) When the hypocrites come to you, they say, “We bear witness that you are indeed the Messenger of Allah” And Allah knows that you are indeed His Messenger, and Allah bears witness that the hypocrites are truly liars.
(2) መሓሎቻቸውን ጋሻ አድርገው ያዙ፡፡ ከአላህም መንገድ ከለከሉ፡፡ እነርሱ ይሠሩት የነበሩት ነገር ከፋ፡፡(2) They have taken their oaths as a shield in order to hinder people from the way of Allah. Evil indeed is what they do!
(3) ይህ እነርሱ (በምላስ) ያመኑ ከዚያም (በልብ) የካዱ በመኾናቸው ነው፡፡ በልቦቻቸውም ላይ ታተመባቸው፤ ስለዚህ እነርሱ አያውቁም፡፡(3) That is because they believed, then disbelieved; therefore their hearts have been sealed, so they do not understand.
(4) ባየሃቸውም ጊዜ አካሎቻቸው (ግዙፍነታቸው) ያስደንቁሃል፡፡ ቢናገሩም ለንግግራቸው ታዳምጣለህ፤ (ከዕውቀት ባዶ በመኾን)፡፡ እነርሱ ልክ በግድግዳ የተጠጉ ግንዶችን ይመስላሉ፡፡ ጩኸትን ሁሉ በእነርሱ ላይ ነው ብለው ያስባሉ፡፡ እነርሱ ጠላቶች ናቸውና ተጠንቀቃቸው፡፡ አላህ ይጋደላቸው፤ (ከእምነት) እንዴት ይመለሳሉ!(4) When you see them, their outward appearance pleases you, and when they speak, you listen to what they say. But they are like planks of wood leaned [against the wall]. They deem every cry to be against them. They are the enemy, so beware of them. May Allah destroy them; how are they deluded?
(5) ለእነሱም ፡- «ኑ የአላህ መልክተኛ ለእናንተ ምሕረትን ይለምንላችኋል፤» በተባሉ ጊዜ ራሶቻቸውን ያዞራሉ፡፡ እነርሱም ትዕቢተኞች ኾነው ሲሸሹ ታያቸዋለህ፡፡(5) When it is said to them, “Come, so that the Messenger of Allah may seek forgiveness for you”, they shake their heads, and you see them turning away in arrogance.
(6) ምሕረትን ብትለምንላቸው ወይም ምሕረትን ባትለምንላቸው በእነርሱ ላይ እኩል ነው፡፡ አላህ ለእነርሱ በፍጹም አይምርም፡፡ አላህ አመጸኞችን ሕዝቦች አየመራምና፡፡(6) It is the same to them whether you seek forgiveness for them or not, Allah will never forgive them. Indeed, Allah does not guide the wicked people.
(7) እነርሱ እነዚያ ፡- «አላህ መልክተኛ ዘንድ ላሉት ሰዎች እስከሚበታተኑ ድረስ አትቀልቡ» የሚሉ ናቸው፡፡ የሰማያትና የምድር ድልቦችም የአላህ ናቸው፡፡ ግን መናፍቃን አያውቁም፡፡(7) They are those who say, “Do not spend on those who are with Allah’s Messenger so that they may desert him. But to Allah belong the treasures of the heavens and earth, but the hypocrites do not understand.
(8) «ወደ መዲና ብንመለስ አሸናፊው ወራዳውን በእርግጥ ከእርሷ ያወጣል» ይላሉ፡፡ አሸናፊነትም ለአላህ፣ ለመልክተኛውና ለምእምናን ነው፡፡ ግን መናፍቃን አያውቁም፡፡(8) They say, “When we return to Madinah, the mightier will surely expel the weaker therefrom.” In fact, all might belongs to Allah and to His Messenger, and to the believers, but the hypocrites do not know.
(9) እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ገንዘቦቻችሁና ልጆቻችሁ አላህን ከማስታወስ አያታሉዋችሁ፡፡ ይህንንም የሚሠሩ ሰዎች እነዚያ እነርሱ ከሳሪዎች ናቸው፡፡(9) O you who believe, do not let your wealth and your children distract you from Allah’s remembrance. For whoever does that, it is they who are the losers.
(10) አንዳችሁንም ሞት ሳይመጣውና ጌታዬ ሆይ! እንድመጸውትና ከደጋጐቹም ሰዎች እንድኾን ወደ ጥቂት ጊዜ ብታቆየኝ ኖሮ እመኛለሁ ከማለቱ በፊት ከሰጠናችሁ ሲሳይ ለግሱ፡፡(10) And spend from what We have provided for you before death comes to one of you, then he would say, “My Lord, If only You had delayed me for a short while, so that I would give in charity and be one of the righteous.”
(11) ማንኛይቱም ነፍስ የሞት ጊዜዋ በመጣበት ጊዜ አላህ በፍጹም አያቆያትም፡፡ አላህም በምትሠሩት ሁሉ ውስጠ ዐዋቂ ነው፡፡(11) But Allah will never delay a soul when its appointed time comes, and Allah is All-Aware of what you do.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

108 – Al-Kawthar

108 – Al-Kawthar (1) እኛ በጣም ብዙ በጎ ነገሮችን ሰጠንህ፡፡ (1) We have surely given you [O Prophet] Al-Kauthar [abundance], (2) ስለዚህ ለጌታህ…

ይህን የአማርኛ ቁርአን ዳውንሎድ ማንበብ ይችላሉ

ይህን የአማርኛ ቁርአን ዳውንሎድ ማንበብ ይችላሉ ይህ የአማርኛ ቋንቋ ቁርአን 239 ገጾችን የያዘ ነው። በአጴ ሃይለስላሴ ጊዜ የታተመው ቁርአን ነው።…

25 – Al -Furqan

25 Al -Furqan (1) ያ ፉርቃንን በባሪያው ላይ ለዓለማት አስፈራሪ ይኾን ዘንድ ያወረደው (አምላክ) ክብርና ጥራት ተገባው፡፡ (1) Blessed is the One…