Default Image
11, Dec 2023
75 – Al-Qiyaama

75 – Al-Qiyaama

(1) (ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡(1) I swear by the Day of Resurrection,
(2) (ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡(2) and I swear by the self-reproaching soul!
(3) ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?(3) Does man think that We cannot reassemble his bones?
(4) አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡(4) In fact, We are able to restore even his very fingertips.
(5) ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡(5) But man desires to persist in his evil ways,
(6) «የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡(6) and asks [mockingly], “When is the Day of Resurrection?”
(7) ዓይንም በዋለለ ጊዜ፡፡(7) But when eyes are dazzled,
(8) ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡(8) and the moon is darkened,
(9) ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡(9) and the sun and the moon are brought together,
(10) «ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡(10) on that Day man will say, “Where is the escape?”
(11) ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡(11) No indeed! There will be no refuge.
(12) በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡(12) On that Day all will end up before your Lord.
(13) ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡(13) On that Day man will be informed of what he has sent forth and left behind.
(14) በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡(14) In fact, man will be a witness against himself,
(15) ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡(15) despite the excuses he may put forward.
(16) በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡(16) Do not move your tongue [O Prophet] in haste trying to memorize it.
(17) (በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡(17) It is upon Us to make you memorize and recite it.
(18) ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡(18) Then when We recite it [through Gabriel], follow its recitation attentively;
(19) ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡(19) then it is upon Us to explain its meanings.
(20) (ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡(20) No indeed! You [people] love this fleeting world,
(21) መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡(21) and neglect the Hereafter.
(22) ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡(22) On that Day some faces will be bright,
(23) ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡(23) looking at their Lord.
(24) ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡(24) And on that Day, some faces will be gloomy,
(25) በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡(25) knowing that a crushing calamity will befall them.
(26) ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤(26) Indeed, when the soul reaches the throat,
(27) «አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡(27) and it is said, “Is there any healer?”
(28) (ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡(28) And he realizes that it is time to depart,
(29) ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡(29) when legs are brought together [in a shroud];
(30) በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ (ፍርድ) ነው፡፡(30) on that Day, he will be driven to your Lord.
(31) አላመነምም አልሰገደምም፡፡(31) He neither believed nor prayed;
(32) ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡(32) rather he denied and turned away,
(33) ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡(33) then went swaggering to his people,
(34) የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡(34) Woe to you [O man], and woe!
(35) ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡(35) Again, woe to you, and woe!
(36) ሰው ስድ ኾኖ መትተውን ይጠረጥራልን?(36) Does man think that he will be left neglected?
(37) የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን?(37) Was he not once a drop of semen emitted,
(38) ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡(38) then he became a clinging clot, then He created him and perfected his form,
(39) ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡(39) and made from him both genders, male and female?
(40) ይህ (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን?(40) Is not He able to bring the dead back to life?

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

16 – An-Nahl

16 – An-Nahl (1) የአላህ ትዕዛዝ መጣ፤ ስለዚህ አታስቸኩሉት፤ ከማይገባው ሁሉ ጠራ ከሚያጋሩትም ሁሉ ላቀ፤ (1) Allah’s decree is coming,…

86 – At-Taariq

86 – At-Taariq (1) በሰማዩ በሌሊት መጪውም እምላለሁ፡፡ (1) By the sky and the night comer – (2) የሌሊት መጪውም…