Default Image
10, Dec 2023
50 – Qaaf

50 – Qaaf

(1) ቀ (ቃፍ) በተከበረው ቁርኣን እምላለሁ (በሙሐመድ አላመኑም)፡፡(1) Qāf. By the Glorious Qur’an!
(2) ይልቁንም ከነሱ ጎሳ የኾነ አስፈራሪ ስለ መጣላቸው ተደነቁ፡፡ ከሓዲዎቹም «ይህ አስደናቂ ነገር ነው» አሉ፡፡(2) But they wonder that a warner has come to them from among themselves, so the disbelievers say, “This is something strange!
(3) «በሞትንና ዐፈር በኾን ጊዜ (እንመለሳለን?) ይህ ሩቅ የኾነ መመለስ ነው፤» (አሉ)፡፡(3) What! Is it when we die and become dust [will we return to life]? That is a far-fetched return.”
(4) ከእነርሱ (አካል) ምድር የምታጎድለውን በእርግጥ ዐውቀናል፡፡ እኛም ዘንድ ጠባቂ መጽሐፍ አልለ፡፡(4) We certainly know what the earth consumes of them [after their death], and with Us is a Preserved Record.
(5) (አልተመለከቱም)፡፡ ይልቁንም በቁርኣን በመጣላቸው ጊዜ አስተባበሉ፡፡ እነርሱም በተማታ ነገር ውሰጥ ናቸው፡፡(5) Rather they rejected the truth when it came to them, so they are in a state of confusion.
(6) ወደ ሰማይም ከበላያቸው ስትኾን ለእርሷ ምንም ቀዳዳዎች የሌሏት ኾና እንዴት እንደ ገነባናትና (በከዋክብት) እንዳጌጥናት አልተመለከቱምን?(6) Have they not then looked at the sky above them – how We built it and adorned it [with stars], and it has no rifts?
(7) ምድርንም ዘረጋናት፡፡ በእርሷም ውስጥ ጋራዎችን ጣልንባት፡፡ በውስጧም ከሚያስደስት ዓይነት ሁሉ አበቀልን፡፡(7) And We have spread out the earth and set therein firm mountains, and caused to grow therein plants of every pleasant kind,
(8) (ይህንን ያደረግነው) ተመላሽ ለኾነ ባሪያ ሁሉ ለማሳየትና ለማስገንዘብ ነው፡፡(8) as a source of insight and a reminder to every slave who turns [to Allah].
(9) ከሰማይም ብሩክን ውሃ አወረድን፡፡ በእርሱም አትክልቶችንና የሚታጨድን (አዝመራ) ፍሬ አበቀልን፡፡(9) And We send down from the sky blessed rain, with which We cause to grow gardens and grain for harvest,
(10) ዘምባባንም ረዣዢም ለእርሷ የተደራረበ እንቡጥ ያላት ስትኾን (አበቀልን)፡፡(10) and towering palm trees having clustered fruit,
(11) ለባሮቹ ሲሳይ ትኾን ዘንድ (አዘጋጀናት)፡፡ በእርሱም የሞተችን አገር ሕያው አደረግንበት፡፡ (ከመቃብር) መውጣትም እንደዚሁ ነው፡፡(11) as a provision for people, and We revive thereby a dead land; likewise will be the resurrection.
(12) ከእነርሱ በፊት የኑሕ ሕዝቦችና የረሰስ ሰዎች፤ ሰሙድም አስተባበሉ፡፡(12) The people of Noah rejected [the truth] before them, as well as the people of the Water-pit of Rass and Thamūd,
(13) ዓድም ፈርዖንም፤ የሉጥ ወንድሞችም፤(13) and so did ‘Ād, Pharaoh, the people of Lot,
(14) የአይከት ሰዎችም የቱብበዕ ሕዝቦችም ሁሉም መልከተኞቹን አስተባበሉ፡፡ ዛቻዬም ተረጋገጠባቸው፡፡(14) and the dwellers of the Forest, and the people of Tubba‘. All of them rejected the messengers, so My warning was fulfilled.
(15) በፊተኛው መፍጠር ደከምን? በእውነቱ እነርሱ ከአዲስ መፍጠር በመጠራጠር ውስጥ ናቸው፡፡(15) Were We wearied by their first creation? No indeed, yet they are in doubt about the second creation.
(16) ሰውንም ነፍሱ (በሐሳቡ) የምታጫውተውን የምናውቅ ስንኾን በእርግጥ ፈጠርነው፤ እኛም ከደም ጋኑ ጅማት ይበልጥ ወደርሱ ቅርብ ነን፡፡(16) We have created man and know what his soul whispers within him, for We are closer to him than his jugular vein.
(17) ሁለቱ ቃል ተቀባዮች (መላእክት) ከቀኝና ከግራ ተቀማጮች ኾነው በሚቀበሉ ጊዜ (አስታውስ)፡፡(17) When the two angel scribes, constantly accompanying him, one on the right, and the other on the left.
(18) ከቃል ምንም አይናገርም በአጠገቡ ተጠባባቂና ዝግጁ የኾኑ (መላእክት) ያሉበት ቢኾን እንጅ፡፡(18) Not a single word he utters but there is with him a vigilant watcher, ready [to record it].
(19) የሞትም መከራ እውነቱን ነገር ታመጣለች፡፡ (ሰው ሆይ)፡- «ይህ ያ ከርሱ ትሸሸው የነበርከው ነው» (ይባላል)፡፡(19) The throes of death will come with the truth. This is what you were trying to avoid.
(20) በቀንዱም ውስጥ ይንነፋል፡፡ ያ (ቀን) የዛቻው (መፈጸሚያ) ቀን ነው፡፡(20) And the Trumpet will be blown; that is the Day of [the given] warning.
(21) ነፍስም ሁሉ ከእርሷ ጋር ነጂና መስካሪ ያለባት ኾና ትመጣለች፡፡(21) Everyone will come, accompanied by an angel to drive him and another to testify.
(22) «ከዚህ ነገር በእርግጥ በዝንጋቴ ውስጥ ነበርክ፡፡ ሺፋንህንም ካንተ ላይ ገለጥንልህ፡፡ ስለዚህ ዛሬ ዓይንህ ስለታም ነው» (ይባላል)፡፡(22) “You were heedless of this; now We have removed your veil, so your vision is sharp Today.”
(23) ቁራኛውም (መልአክ) «ይህ ያ እኔ ዘንድ ያለው ቀራቢ ነው» ይላል፡፡(23) His angel-companion will say, “Here is the record ready with me.”
(24) «ሞገደኛ ከሓዲን ሁሉ በገሀነም ውስጥ ጣሉ፡፡»(24) [It will be said to the two angels], “Throw into Hell every obstinate disbeliever,
(25) «ለበጎ ሥራ ከልካይ፣ በዳይ፣ ተጠራጣሪ የኾነን ሁሉ፤» (ጣሉ)፡፡(25) every withholder of good, transgressor, and doubter,
(26) «ያንን ከአላህ ጋር ሌላን አምላክ ያደረገውን በብርቱ ቅጣት ውስጥ ጣሉት፤» (ይባላል)፡፡(26) who set up with Allah another god. Throw him into the severe punishment.”
(27) ቁራኛው (ሰይጣን) «ጌታችን ሆይ! እኔ አላሳሳትኩትም፡፡ ግን (ራሱ) በሩቅ ስሕተት ውስጥ ነበር» ይላል፡፡(27) His [devil] companion will say, “Our Lord, I did not mislead him, but he himself was far astray.”
(28) (አላህ) «ወደእናንተ ዛቻን በእርግጥ ያስቀደምኩ ስኾን እኔ ዘንድ አትጨቃጨቁ» ይላቸዋል፡፡(28) Allah will say, “Do not argue in My presence, for I had already given you the warning.
(29) «ቃሉ እኔ ዘንድ አይለወጥም፡፡ እኔም ለባሮቼ ፈጽሞ በዳይ አይደለሁም» (ይላቸዋል)፡፡(29) My Word cannot be changed, nor am I unjust to My slaves.”
(30) ለገሀነም «ሞላሽን? የምንልበትንና ጭማሪ አለን? የምትልበትን ቀን» (አስጠንቅቃቸው)፡፡(30) [Beware of] the Day when We will say to Hell, “Have you reached your fill?” It will say, “Are there any more?”
(31) ገነትም አላህን ለፈሩት እሩቅ ባልኾነ ስፍራ ትቅቀረባለች፡፡(31) Paradise will be brought near to the righteous, not far off.
(32) «ይህ ወደ አላህ ተመላሽና (ሕግጋቱን) ጠባቂ ለኾነ ሁሉ የተቀጠራችሁት ነው» (ይባላሉ)፡፡(32) [It will be said], “This is what you were promised; this is for everyone who constantly turned [to Allah] and was dutiful,
(33) «አልረሕማንን በሩቁ ኾኖ ለፈራና በንጹሕ ልብ ለመጣ» (ትቅቀረባለች)፡፡(33) who feared the Most Compassionate unseen, and came with a devoted heart.
(34) «በሰላም ግቧት ይህ የመዘውተሪያ ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡(34) Enter it in peace. This is the Day of eternity.”
(35) ለነርሱ በውስጧ ሲኾኑ የሚሹት ሁሉ አልላቸው፡፡ እኛም ዘንድ ጭማሪ አልለ፡፡(35) They will have therein all what they wish for, and We have yet more.
(36) ከእነርሱም (ከቁረይሾች) በፊት ከክፍለ ዘመናት ሕዝቦች ብዙዎችን እነርሱ በኀያልነት ከእነርሱ ይበልጥ የበረቱ የኾኑትን (ማምለጫ ፍለጋ) በየአገሮቹም የመረመሩትን አጥፍተናል፡፡ ማምለጫ አለን?(36) How many nations We destroyed before them [Makkans] who were stronger than them in might! They traveled through the land. Did they find any escape?
(37) በዚህ ውሰጥ ለእርሱ ልብ ላለው ወይም እርሱ (በልቡ) የተጣደ ኾኖ (ወደሚነበብለት) ጆሮውን ለጣለ ሰው ግሳጼ አለበት፡፡(37) Indeed, in that is a reminder for anyone who has a [mindful] heart or lends an attentive ear.
(38) ሰማያትንና ምድርን በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ በእርግጥ ፈጠርን፡፡ ድካምም ምንም አልነካንም፡፡(38) Indeed, We created the heavens and earth and all that is between them in six days, and no weariness touched Us.
(39) በሚሉትም ላይ ታገሥ፤ ጌታህንም ከማመስገን ጋር ፀሐይ ከመውጣቷ በፊት ከመግባቷም በፊት አወድሰው፡፡(39) So bear patiently [O Prophet] what they say, and glorify the praise of your Lord before sunrise and before sunset.
(40) ከሌሊቱም አወድሰው ከስግደቶችም በኋላዎች (አወድሰው)፡፡(40) And glorify Him in the night and after the prayers.
(41) (የሚነገርህን) አዳምጥም፡፡ ጠሪው ከቅርብ ስፍራ በሚጠራበት ቀን (ከመቃብራቸው ይወጣሉ)፡፡(41) And listen! On the Day when the Caller will call out from a nearby place,
(42) ጩኸቲቱን በእውነት የሚሰሙበት ቀን ያ (ከመቃብር) የመውጫው ቀን ነው፡፡(42) the Day when they will hear the Blast [of the second Trumpet] in truth. That is the Day of resurrection.
(43) እኛ እኛው ሕያው እናደርጋለን፡፡ እንገድላለንም፡፡ መመለሻም ወደእኛ ብቻ ነው፡፡(43) Indeed, it is We Who give life and cause death, and to Us is the final return.
(44) የሚፈጥኑ ኾነው ምድር ከእነርሱ ላይ የምትሰነጣጠቅበት ቀን (የመውጫው ቀን ነው)፡፡ ይህ በእኛ ላይ ገር የኾነ መሰብሰብ ነው፡፡(44) On the Day when the earth will be rent asunder for them as they hasten forth [from their graves]; that is an easy gathering for Us.
(45) እኛ የሚሉትን ሁሉ ዐዋቂ ነን፡፡ አንተም በእነርሱ ላይ አስገዳጅ አይደለህም፡፡ ስለዚህ ዛቻየን የሚፈራን ሰው በቁርኣን አስታውስ፡፡(45) We know best what they say, and you are not there to compel them to believe. But remind with the Qur’an those who fear My warning.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Related Posts

ሱረቱ ኒሳዕ አማርኛ ቁርአን An-Nisaa Amharic Qurna

ሱረቱ ኒሳዕ አማርኛ ቁርአን An-Nisaa Amharic Qurna يَا أَيُّهَا النَّاسُ اتَّقُوا رَبَّكُمُ الَّذِي خَلَقَكُم مِّن نَّفْسٍ وَاحِدَةٍ وَخَلَقَ مِنْهَا زَوْجَهَا…

47 – Muhammad

47 – Muhammad (1) እነዚያ የካዱ ከአላህ መንገድም የከለከሉ (አላህ) ሥራዎቻቸውን አጠፋባቸው፡፡ (1) Those who disbelieve and prevent others from Allah’s way,…

ሱረቱል አል-በቀራህ አማርኛ ቅዱስ ቁርአን ምዕራፍ 2 Amharic Quran

ሱረቱል አል-በቀራህ አማርኛ ቅዱስ ቁርአን ምዕራፍ 2 Amharic Quran بِسۡمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحۡمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ Bismillah hir rahman nir raheem الم  [1] (1) አ.ለ.መ    (1)…