Default Image
20, Nov 2023
ሱረቱ አል ሒጅር አማርኛ ቁርአን // Free Amharic Quran Suretu Al-Hijr

ሱረቱ አል ሒጅር አማርኛ ቁርአን // Free Amharic Quran Suretu Al-Hijr

الر ۚ تِلْكَ آيَاتُ الْكِتَابِ وَقُرْآنٍ مُّبِينٍ  [1]

(1) አ.ለ.ረ (አሊፍ ላም ራ) ይህች (አናቅጽ) ከመጽሐፉ አንቀጾችና ገላጭ ከኾነው ቁርኣን ናት፡፡

(1) Alif Lām Ra. These are the verses of the Book and a clear Qur’an.

رُّبَمَا يَوَدُّ الَّذِينَ كَفَرُوا لَوْ كَانُوا مُسْلِمِينَ  [2]

(2) እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ ቀን) ሙስሊሞች በኾኑ ኖሩ በብዛት ይመኛሉ፡፡

(2) There will come a time that the disbelievers will wish that they were Muslims.

ذَرْهُمْ يَأْكُلُوا وَيَتَمَتَّعُوا وَيُلْهِهِمُ الْأَمَلُ ۖ فَسَوْفَ يَعْلَمُونَ  [3]

(3) ተዋቸው ይብሉ፤ ይጠቀሙም፡፡ ተስፋም ያዘናጋቸው፡፡ በእርግጥም (መጥፎ ፍጻሜያቸውን) ያውቃሉ፡፡

(3) Let them eat and enjoy themselves and be diverted with false hope; they will come to know.

وَمَا أَهْلَكْنَا مِن قَرْيَةٍ إِلَّا وَلَهَا كِتَابٌ مَّعْلُومٌ  [4]

(4) ማንኛይቱንም ከተማ ለእርሷ የተወሰነ መጽሐፍ (ጊዜያት) ያላት ኾና እንጂ አላጠፋንም፡፡

(4) We never destroyed any town except that it had a destined time.

مَّا تَسْبِقُ مِنْ أُمَّةٍ أَجَلَهَا وَمَا يَسْتَأْخِرُونَ  [5]

(5) ማንኛይቱም ሕዝብ ጊዜዋን ምንም አትቀድምም፡፡ (ከእርሱ) አይቆዩምም፡፡

(5) No nation can advance its appointed time, nor can they delay it.

وَقَالُوا يَا أَيُّهَا الَّذِي نُزِّلَ عَلَيْهِ الذِّكْرُ إِنَّكَ لَمَجْنُونٌ  [6]

(6) «አንተ ያ በእርሱ ላይ ቁርኣን የተወረደለት ሆይ! አንተ በእርግጥ ዕብድ ነህ» አሉም፡፡

(6) They say, “O you to whom the Reminder has been sent down, You are surely insane!

لَّوْ مَا تَأْتِينَا بِالْمَلَائِكَةِ إِن كُنتَ مِنَ الصَّادِقِينَ  [7]

(7) «ከእውነተኞቹ እንደ ኾንክ በመላእክት (መስካሪ) ለምን አትመጣንም» (አሉ)፡፡

(7) Why do you not bring us the angels, if you are truthful?”

مَا نُنَزِّلُ الْمَلَائِكَةَ إِلَّا بِالْحَقِّ وَمَا كَانُوا إِذًا مُّنظَرِينَ  [8]

(8) መላእክትን በእውነት (በቅጣት) እንጂ አናወርድም፡፡ ያን ጊዜም የሚቆዩ አይደሉም፡፡

(8) We do not send down the angels except for a just cause, and then they [the disbelievers] would be granted no respite.

إِنَّا نَحْنُ نَزَّلْنَا الذِّكْرَ وَإِنَّا لَهُ لَحَافِظُونَ  [9]

(9) እኛ ቁርኣንን እኛው አወረድነው፡፡ እኛም ለእርሱ ጠባቂዎቹ ነን፡፡

(9) It is We Who have sent down the Reminder, and it is We Who will preserve it.

وَلَقَدْ أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ فِي شِيَعِ الْأَوَّلِينَ  [10]

(10) ከአንተም በፊት በነበሩት በመጀመሪያዎቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልክተኞችን) በእርግጥ ልከናል፡፡

(10) We did send messengers before you among the factions of early peoples.

وَمَا يَأْتِيهِم مِّن رَّسُولٍ إِلَّا كَانُوا بِهِ يَسْتَهْزِئُونَ  [11]

(11) ማንኛውም መልእክተኛ በእርሱ የሚያላግጡበት ኾነው እንጅ አይመጣቸውም ነበር፡፡

(11) No messenger came to them except that they ridiculed him.

كَذَٰلِكَ نَسْلُكُهُ فِي قُلُوبِ الْمُجْرِمِينَ  [12]

(12) እንደዚሁ (ማስተባበልን) በአመጸኞቹ ልቦች ውስጥ እናገባዋለን፡፡

(12) This is how We let this [denial] enter the hearts of the wicked.

لَا يُؤْمِنُونَ بِهِ ۖ وَقَدْ خَلَتْ سُنَّةُ الْأَوَّلِينَ  [13]

(13) በእርሱ አያምኑበትም፡፡ የቀድሞዎቹም ድርጊት በእርግጥ አልፋለች፤ (እንደጠፉ ይጠፋሉ)፡፡

(13) They will not believe in it, although the examples of the earlier people are well established.

وَلَوْ فَتَحْنَا عَلَيْهِم بَابًا مِّنَ السَّمَاءِ فَظَلُّوا فِيهِ يَعْرُجُونَ  [14]

(14) በእነርሱም ላይ ከሰማይ ደጃፍን በከፈትንላቸውና በእርሱ ሲወጡ በዋሉ ኖሮ፤

(14) Even if We were to open for them a gateway to the heaven, through which they kept ascending,

لَقَالُوا إِنَّمَا سُكِّرَتْ أَبْصَارُنَا بَلْ نَحْنُ قَوْمٌ مَّسْحُورُونَ  [15]

(15) «የተዘጉት ዓይኖቻችን ናቸው፡፡ እንዲያውም እኛ የተደገመብን ሰዎች ነን» ባሉ ነበር፡፡

(15) they would still say, “Our eyes have been dazzled; rather, we have been bewitched.”

وَلَقَدْ جَعَلْنَا فِي السَّمَاءِ بُرُوجًا وَزَيَّنَّاهَا لِلنَّاظِرِينَ  [16]

(16) በሰማይም ላይ ቡርጆችን በእርግጥ አድርገናል፡፡ ለተመልካቾችም (በከዋክብት) አጊጠናታል፡፡

(16) We have placed constellations in the heaven and adorned it for the onlookers,

وَحَفِظْنَاهَا مِن كُلِّ شَيْطَانٍ رَّجِيمٍ  [17]

(17) ከተባረረ ሰይጣንም ሁሉ ጠብቀናታል፡፡

(17) and We have guarded it from every accursed devil,

إِلَّا مَنِ اسْتَرَقَ السَّمْعَ فَأَتْبَعَهُ شِهَابٌ مُّبِينٌ  [18]

(18) ግን (ወሬ) መስማትን የሚሰርቅ ወዲየውኑ አብሪ ችቦ ይከተለዋል፡፡ (ያቃጥለዋል)፡፡

(18) except the one who manages to eavesdrop, he will then be pursued by a visible burning flame.

وَالْأَرْضَ مَدَدْنَاهَا وَأَلْقَيْنَا فِيهَا رَوَاسِيَ وَأَنبَتْنَا فِيهَا مِن كُلِّ شَيْءٍ مَّوْزُونٍ  [19]

(19) ምድርንም ዘረጋናት፡፡ በውስጧም ኮረብታዎችን ጣልናባት፡፡ በውስጧም (የተለካን) በቃይ ሁሉ አበቀልንባት፡፡

(19) As for the earth, We have spread it out and placed therein firm mountains, and caused to grow therein everything in due proportion.

وَجَعَلْنَا لَكُمْ فِيهَا مَعَايِشَ وَمَن لَّسْتُمْ لَهُ بِرَازِقِينَ  [20]

(20) በእርሷም ውስጥ ለእናንተ መኖሪያዎችንና ለእርሱ መጋቢዎቹ ያልኾናችሁትንም (እንስሳትን) አደረግንላችሁ፡፡

(20) And We have made therein for you means of sustenance and for those whom you do not provide.

وَإِن مِّن شَيْءٍ إِلَّا عِندَنَا خَزَائِنُهُ وَمَا نُنَزِّلُهُ إِلَّا بِقَدَرٍ مَّعْلُومٍ  [21]

(21) መካዚኖቹም (መክፈቻቸው) እኛ ዘንድ ያልሆነ ምንም ነገር የለም፡፡ በተወሰነም ልክ እንጂ አናወርደውም፡፡

(21) There is nothing except that We have its treasuries, and We do not send it down except in a determined measure.

وَأَرْسَلْنَا الرِّيَاحَ لَوَاقِحَ فَأَنزَلْنَا مِنَ السَّمَاءِ مَاءً فَأَسْقَيْنَاكُمُوهُ وَمَا أَنتُمْ لَهُ بِخَازِنِينَ  [22]

(22) ነፋሶችንም (ደመናን) ተሸካሚዎች አድርገን ላክን፡፡ ከሰማይም (ከደመና) ዝናብን አወረድን፡፡ እርሱንም አጠጣናችሁ፡፡ እናንተም ለእርሱ አድላቢዎች አይደላችሁም፡፡

(22) And We send fertilizing winds, and send down rain from the sky for you to drink, and it is not you who could store it.

وَإِنَّا لَنَحْنُ نُحْيِي وَنُمِيتُ وَنَحْنُ الْوَارِثُونَ  [23]

(23) እኛም ሕያው የምናደርግና የምንገድል እኛው ብቻ ነን፡፡ እኛም (ፍጡርን ሁሉ ) የምንወርስ (ቀሪ) ነን፡፡

(23) Indeed, it is We Who give life and cause death, and We are the Inheritors [of all things].

وَلَقَدْ عَلِمْنَا الْمُسْتَقْدِمِينَ مِنكُمْ وَلَقَدْ عَلِمْنَا الْمُسْتَأْخِرِينَ  [24]

(24) ከእናንተም ተቀዳሚዎቹን በእርግጥ ዐውቀናል፡፡ ወደ ኋላም ቀሪዎቹን በእርግጥ ዐውቀናል፡፡

(24) We surely know those of you who have gone before and those who are yet to come.

وَإِنَّ رَبَّكَ هُوَ يَحْشُرُهُمْ ۚ إِنَّهُ حَكِيمٌ عَلِيمٌ  [25]

(25) ጌታህም እርሱ ይሰበስባችኋል፡፡ እርሱ ጥበበኛ ዐዋቂ ነውና፡፡

(25) It is your Lord Who will gather them together. He is All-Wise, All-Knowing.

وَلَقَدْ خَلَقْنَا الْإِنسَانَ مِن صَلْصَالٍ مِّنْ حَمَإٍ مَّسْنُونٍ  [26]

(26) ሰውንም ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከሚገማ ጥቁር ጭቃ በእርግጥ ፈጠርነው፡፡

(26) We have created man from sounding clay, made of aging mud.

وَالْجَانَّ خَلَقْنَاهُ مِن قَبْلُ مِن نَّارِ السَّمُومِ  [27]

(27) ጃንንም (ከሰው) በፊት ከእሳት ነበልባል ፈጠርነው፡፡

(27) And the jinn We created before that, from smokeless fire.

وَإِذْ قَالَ رَبُّكَ لِلْمَلَائِكَةِ إِنِّي خَالِقٌ بَشَرًا مِّن صَلْصَالٍ مِّنْ حَمَإٍ مَّسْنُونٍ  [28]

(28) ጌታህም ለመላእክት ባለጊዜ (አስታውስ)፡፡ እኔ ሰውን ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከሚገማ ጭቃ እፈጥራለሁ፡፡

(28) And [remember] when your Lord said to the angels, “I am going to create a human being from sounding clay, made of aging mud.

فَإِذَا سَوَّيْتُهُ وَنَفَخْتُ فِيهِ مِن رُّوحِي فَقَعُوا لَهُ سَاجِدِينَ  [29]

(29) (ፍጥረቱን) ባስተካከልኩትና በውስጡ ከመንፈሴ በነፋሁበትም ጊዜ ለእርሱ ሰጋጆች ኾናችሁ ውደቁ፡፡

(29) When I have shaped him and breathed into him of My spirit, then fall down before him in prostration.”

فَسَجَدَ الْمَلَائِكَةُ كُلُّهُمْ أَجْمَعُونَ  [30]

(30) መላእክትም መላውም ተሰብስበው ሰገዱ፡፡

(30) Thereupon, all of the angels fell down in prostration,

إِلَّا إِبْلِيسَ أَبَىٰ أَن يَكُونَ مَعَ السَّاجِدِينَ  [31]

(31) ኢብሊስ (ዲያብሎስ) ብቻ ሲቀር፡፡ ከሰጋጆቹ ጋር ከመኾን እንቢ አለ፡፡

(31) except Iblīs, who refused to be with those who prostrated.

قَالَ يَا إِبْلِيسُ مَا لَكَ أَلَّا تَكُونَ مَعَ السَّاجِدِينَ  [32]

(32) (አላህም) «ኢብሊስ ሆይ! ከሰጋጆቹ ጋር የማትኾን ላንተ ምን ምክንያት አለህ» አለው፡፡

(32) Allah said, “O Iblīs, what is the matter with you that you were not with those who prostrated?”

قَالَ لَمْ أَكُن لِّأَسْجُدَ لِبَشَرٍ خَلَقْتَهُ مِن صَلْصَالٍ مِّنْ حَمَإٍ مَّسْنُونٍ  [33]

(33) «ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከግም ጭቃ ለፈጠርከው ሰው ልሰግድ አይገባኝም» አለ፡፡

(33) He said, “I am not such to prostrate before a human whom You created from sounding clay, made of aging mud.”

قَالَ فَاخْرُجْ مِنْهَا فَإِنَّكَ رَجِيمٌ  [34]

(34) (አላህ) አለው «ከርሷም ውጣ፡፡ አንተ የተባረርክ እርጉም ነህና፡፡»

(34) He said, “Then get out of here, for you are accursed,

وَإِنَّ عَلَيْكَ اللَّعْنَةَ إِلَىٰ يَوْمِ الدِّينِ  [35]

(35) «ባንተ ላይም እስከ ፍርዱ ቀን ድረስ እርግማን አለብህ፡፡»

(35) and the curse will be upon you until the Day of Judgment.”

قَالَ رَبِّ فَأَنظِرْنِي إِلَىٰ يَوْمِ يُبْعَثُونَ  [36]

(36) «ጌታዬ ሆይ! እንግዲውያስ (ሰዎች) እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ አቆየኝ» አለ፡፡

(36) Iblīs said, “My Lord, then grant me respite until the Day they are resurrected.”

قَالَ فَإِنَّكَ مِنَ الْمُنظَرِينَ  [37]

(37) (አላህም) አለ «አንተ ከሚቆዩት ነህ፡፡

(37) Allah said, “You are of those who are granted respite,

إِلَىٰ يَوْمِ الْوَقْتِ الْمَعْلُومِ  [38]

(38) «እስከታወቀው ወቅት ቀን ድረስ፡፡»

(38) until the Day of the Appointed Time.”

قَالَ رَبِّ بِمَا أَغْوَيْتَنِي لَأُزَيِّنَنَّ لَهُمْ فِي الْأَرْضِ وَلَأُغْوِيَنَّهُمْ أَجْمَعِينَ  [39]

(39) (ኢብሊስ) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔን በማጥመምህ ይኹንብኝ ለነርሱ በምድር ላይ (ኀጢአትን) እሸልምላቸዋለሁ፡፡ ሁሉንም አጠማቸዋለሁም፡፡»

(39) He said, “My Lord, since You have sent me astray, I will surely make [sins] alluring to them on earth and mislead them all,

إِلَّا عِبَادَكَ مِنْهُمُ الْمُخْلَصِينَ  [40]

(40) «ከነርሱ ፍጹሞቹ ባሮችህ ብቻ ሲቀሩ፡፡»

(40) except Your chosen slaves among them.”

قَالَ هَٰذَا صِرَاطٌ عَلَيَّ مُسْتَقِيمٌ  [41]

(41) (አላህም) አለ «ይህ በእኔ ላይ (መጠበቁ የተገባ) ቀጥተኛ መንገድ ነው፡፡»

(41) Allah said, “This is a straight path leading to Me.

إِنَّ عِبَادِي لَيْسَ لَكَ عَلَيْهِمْ سُلْطَانٌ إِلَّا مَنِ اتَّبَعَكَ مِنَ الْغَاوِينَ  [42]

(42) «እነሆ ባሮቼ በእነሱ ላይ ላንተ ስልጣን የለህም፡፡ ከጠማሞቹ የተከተለህ ሰው ብቻ ሲቀር፡፡»

(42) You will have no authority over My slaves, except the deviants who follow you.

وَإِنَّ جَهَنَّمَ لَمَوْعِدُهُمْ أَجْمَعِينَ  [43]

(43) «ገሀነምም (ለርሱና ለተከተሉት) ለመላውም በእርግጥ ቀጠሯቸው ናት፡፡

(43) And Hell is certainly the promised place for them, all together.

لَهَا سَبْعَةُ أَبْوَابٍ لِّكُلِّ بَابٍ مِّنْهُمْ جُزْءٌ مَّقْسُومٌ  [44]

(44) «ለእርሷ ሰባት ደጃፎች አሏት፡፡ ለየደጀፉም ሁሉ ከእነሱ የተከፈለ ፋንታ አለ፡፡

(44) It has seven gates; each gate will have its allotted share of them.”

إِنَّ الْمُتَّقِينَ فِي جَنَّاتٍ وَعُيُونٍ  [45]

(45) «እነዚያ (ከኀጢአት) የተጠነቀቁት በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡

(45) The righteous will be in gardens and springs.

ادْخُلُوهَا بِسَلَامٍ آمِنِينَ  [46]

(46) «ጸጥተኞች ኾናችሁ በሰላም ግቧት (ይባላሉ)፡፡

(46) “Enter in peace and safety!”

وَنَزَعْنَا مَا فِي صُدُورِهِم مِّنْ غِلٍّ إِخْوَانًا عَلَىٰ سُرُرٍ مُّتَقَابِلِينَ  [47]

(47) «ባልጋዎችም ላይ ፊት ለፊት የሚቅጣጩ ወንድማማቾች ኾነው በደረቶቻቸው ውስጥ ከቂም ያለውን ሁሉ እናስወግዳለን፡፡

(47) We will remove all ill feelings from their hearts; like brothers, seated on couches facing one another.

لَا يَمَسُّهُمْ فِيهَا نَصَبٌ وَمَا هُم مِّنْهَا بِمُخْرَجِينَ  [48]

(48) «በእርሷም ውስጥ ድካም አይነካቸውም፡፡ እነሱም ከእርሷ የሚወጡ አይደሉም፡፡»

(48) No fatigue will ever touch them therein, nor will they ever be made to leave.

نَبِّئْ عِبَادِي أَنِّي أَنَا الْغَفُورُ الرَّحِيمُ  [49]

(49) ባሮቼን እኔ መሓሪው አዛኙ እኔው ብቻ መኾኔን ንገራቸው፡፡

(49) Inform My slaves that I am indeed the All-Forgiving, the Most Merciful,

وَأَنَّ عَذَابِي هُوَ الْعَذَابُ الْأَلِيمُ  [50]

(50) ቅጣቴም እርሱ አሳማሚ ቅጣት መኾኑን (ንገራቸው)፡፡

(50) and that My punishment is the most painful punishment.

وَنَبِّئْهُمْ عَن ضَيْفِ إِبْرَاهِيمَ  [51]

(51) ከኢብራሂም እንግዶችም (ወሬ) ንገራቸው፡፡

(51) And inform them about the guests of Abraham.

إِذْ دَخَلُوا عَلَيْهِ فَقَالُوا سَلَامًا قَالَ إِنَّا مِنكُمْ وَجِلُونَ  [52]

(52) በእርሱ ላይ በገቡና ሰላም ባሉት ጊዜ የኾነውን (አስታውስ)፡፡ (እርሱም) «እኛ ከእናንተ ፈሪዎች ነን» አላቸው፡፡

(52) When they entered upon him and said, “Peace!” He said, “We are afraid of you.”

قَالُوا لَا تَوْجَلْ إِنَّا نُبَشِّرُكَ بِغُلَامٍ عَلِيمٍ  [53]

(53) «አትፍራ፤ እኛ ዐዋቂ በኾነ ወንድ ልጅ እናበስርሃለን» አሉት፡፡

(53) They said, “Do not be afraid; We give you glad tidings of a knowledgeable boy.”

قَالَ أَبَشَّرْتُمُونِي عَلَىٰ أَن مَّسَّنِيَ الْكِبَرُ فَبِمَ تُبَشِّرُونَ  [54]

(54) «እርጅና የደረሰብኝ ከመኾኔ ጋር አበሰራችሁኝን በምን ታበስሩኛላችሁ» አለ፡፡

(54) He said, “Do you give me glad tidings despite my old age? What glad tidings are you giving me?”

قَالُوا بَشَّرْنَاكَ بِالْحَقِّ فَلَا تَكُن مِّنَ الْقَانِطِينَ  [55]

(55) «በእውነት አበሰርንህ፡፡ ከተሰፋ ቆራጮችም አትኹን» አሉ፡፡

(55) They said, “We have given you glad tidings in truth, so do not be of those who despair.”

قَالَ وَمَن يَقْنَطُ مِن رَّحْمَةِ رَبِّهِ إِلَّا الضَّالُّونَ  [56]

(56) «ከጠማማዎችም በስተቀር ከጌታው እዝነት ተስፋን የሚቆርጥ ማነው» አለ፡፡

(56) He said, “Who would despair of his Lord’s mercy except those who are misguided?”

قَالَ فَمَا خَطْبُكُمْ أَيُّهَا الْمُرْسَلُونَ  [57]

(57) «እናንተ መልክተኞች ሆይ! ኧረ ለመኾኑ ነገራችሁ ምንድን ነው» አለ፡፡

(57) He said, “So, what is your mission, O messengers?”

قَالُوا إِنَّا أُرْسِلْنَا إِلَىٰ قَوْمٍ مُّجْرِمِينَ  [58]

(58) «እኛ አመጸኞች ወደ ኾኑ ሕዝቦች ተልከናል» አሉት፡፡

(58) They said, “We have been sent to a wicked people,

إِلَّا آلَ لُوطٍ إِنَّا لَمُنَجُّوهُمْ أَجْمَعِينَ  [59]

(59) «የሉጥ ቤተሰቦች ብቻ ሲቀሩ፡፡ (እነርሱን) እኛ ሁላቸውንም በእርግጥ የምናድናቸው ነን፡፡

(59) except the household of Lot; we will surely save them all,

إِلَّا امْرَأَتَهُ قَدَّرْنَا ۙ إِنَّهَا لَمِنَ الْغَابِرِينَ  [60]

(60) «ሚስቱ ብቻ ስትቀር፡፡ እርሷን (በቅጣቱ ውስጥ) ከሚቀሩት መኾኗን ወሰነናል» (አሉ)፡፡

(60) except his wife; We have decreed that she will be among those who stay behind.”

فَلَمَّا جَاءَ آلَ لُوطٍ الْمُرْسَلُونَ  [61]

(61) መልክተኞቹም የሉጥን ቤተሰቦች በመጡባቸው ጊዜ፤

(61) When the messengers came to the household of Lot,

قَالَ إِنَّكُمْ قَوْمٌ مُّنكَرُونَ  [62]

(62) (ሉጥ) «እናንተ የተሳታችሁ ሕዝቦች ናችሁ» አላቸው፡፡

(62) he said, “You are an unfamiliar people.”

قَالُوا بَلْ جِئْنَاكَ بِمَا كَانُوا فِيهِ يَمْتَرُونَ  [63]

(63) «አይደለም እኛ ሕዝቦችህ በርሱ ይጠራጠሩበት በነበሩት ቅጣት መጣንህ» አሉት፡፡

(63) They said, “We have come to you with that [punishment] which they have doubted.

وَأَتَيْنَاكَ بِالْحَقِّ وَإِنَّا لَصَادِقُونَ  [64]

(64) «እውነትንም ይዘን መጣንህ፡፡ እኛም በእርግጥ እውነተኞች ነን፡፡

(64) We have come to you with the truth, and we are certainly truthful.

فَأَسْرِ بِأَهْلِكَ بِقِطْعٍ مِّنَ اللَّيْلِ وَاتَّبِعْ أَدْبَارَهُمْ وَلَا يَلْتَفِتْ مِنكُمْ أَحَدٌ وَامْضُوا حَيْثُ تُؤْمَرُونَ  [65]

(65) ከቤተሰብህም ጋር በሌሊቱ ከፊል ኺድ፡፡ ከኋላቸውም ተከተል፡፡ ከእናንተም አንድም ሰው ወደ ኋላው አይገላመጥ፡፡ ወደ ታዘዛችሁበትም ስፍራ እለፉ» (አሉት)፡፡

(65) So travel with your household in the dark of night and go behind them; none of you should look back, and keep going to where you are commanded.”

وَقَضَيْنَا إِلَيْهِ ذَٰلِكَ الْأَمْرَ أَنَّ دَابِرَ هَٰؤُلَاءِ مَقْطُوعٌ مُّصْبِحِينَ  [66]

(66) ወደርሱም ያንን ትእዛዝ አወረድን፡፡ (እርሱም) የእነዚህ (ሕዝቦች) መጨረሻ ያነጉ ሲኾኑ (ሥራቸው) መቆረጥ ነው፡፡

(66) We conveyed this decree to him that these [people] will be exterminated by early morning.”

وَجَاءَ أَهْلُ الْمَدِينَةِ يَسْتَبْشِرُونَ  [67]

(67) የከተማይቱም ሰዎች የሚበሳሰሩ ኾነው መጡ፡፡

(67) The people of the city came [to Lot] rejoicing.

قَالَ إِنَّ هَٰؤُلَاءِ ضَيْفِي فَلَا تَفْضَحُونِ  [68]

(68) (ሉጥም) አለ «እነዚህ እንግዶቼ ናቸውና አታጋልጡኝ፡፡

(68) Lot said, “These are my guests, so do not bring shame on me.

وَاتَّقُوا اللَّهَ وَلَا تُخْزُونِ  [69]

(69) «አላህንም ፍሩ፤ አታሳፍሩኝም፡፡»

(69) Fear Allah and do not disgrace me.”

قَالُوا أَوَلَمْ نَنْهَكَ عَنِ الْعَالَمِينَ  [70]

(70) «ከዓለማት (ማንንም እንዳታስተናግድ) አልከለከልንህምን» አሉት፡፡

(70) They said, “Did we not forbid you from [protecting] people?”

قَالَ هَٰؤُلَاءِ بَنَاتِي إِن كُنتُمْ فَاعِلِينَ  [71]

(71) (ሉጥም) «እነኝህ ሴቶች ልጆቼ ናቸው፡፡ ሠሪዎች ብትኾኑ (አግቧቸው)» አለ፡፡

(71) He said, “These are my daughters [to marry] if you must.”

لَعَمْرُكَ إِنَّهُمْ لَفِي سَكْرَتِهِمْ يَعْمَهُونَ  [72]

(72) በዕድሜህ እንምላለን እነሱ በእርግጥ በስከራቸው ውስጥ ይዋልላሉ፡፡

(72) By your life [O prophet], they were wandering blindly in their intoxication [of lust].

فَأَخَذَتْهُمُ الصَّيْحَةُ مُشْرِقِينَ  [73]

(73) ጩኸቲቱም ፀሐይ የወጣችባቸው ሲኾኑ ያዘቻቸው፡፡

(73) So they were seized by the blast at sunrise,

فَجَعَلْنَا عَالِيَهَا سَافِلَهَا وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهِمْ حِجَارَةً مِّن سِجِّيلٍ  [74]

(74) ላይዋንም ከታችዋ አደረግን፡፡ በእነሱም ላይ የሸክላ ደንጊያዎችን አዘነብንባቸው፡፡

(74) and We turned their cities upside down and rained down on them stones of baked clay.

إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَاتٍ لِّلْمُتَوَسِّمِينَ  [75]

(75) በዚህ ውስጥ ለተመልካቾች በእርግጥ መገምገሚያዎች አሉበት፡፡

(75) Indeed, there are signs in this for those who discern.

وَإِنَّهَا لَبِسَبِيلٍ مُّقِيمٍ  [76]

(76) እሷም (ከተማይቱ) በቀጥታ መንገድ ላይ ናት፡፡

(76) And their place is located by a known route.

إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً لِّلْمُؤْمِنِينَ  [77]

(77) በዚህ ውስጥ በእርግጥ ለምእምናን መገሰጫ አለ፡፡

(77) Indeed, there are signs in this for the believers.

وَإِن كَانَ أَصْحَابُ الْأَيْكَةِ لَظَالِمِينَ  [78]

(78) እነሆ የአይከት ሰዎችም በእርግጥ በዳዮች ነበሩ፤

(78) And the people of the Forest [of Shu‘ayb] were wrongdoers.

فَانتَقَمْنَا مِنْهُمْ وَإِنَّهُمَا لَبِإِمَامٍ مُّبِينٍ  [79]

(79) ከነሱም ተበቀልን ሁለቱም (የሉጥና የአይከት ሕዝቦች ከተሞች) በእርግጥ በግልጽ መንገድ ላይ ናቸው፡፡

(79) So We punished them in retribution, and both [places] are by a clear highway.

وَلَقَدْ كَذَّبَ أَصْحَابُ الْحِجْرِ الْمُرْسَلِينَ  [80]

(80) የሒጅርም ሰዎች መልክተኞቹን በእርግጥ አስተባበሉ፡፡

(80) Surely the people of Al-Hijr [Thamūd] also rejected the messengers.

وَآتَيْنَاهُمْ آيَاتِنَا فَكَانُوا عَنْهَا مُعْرِضِينَ  [81]

(81) ተዓምራታችንንም ሰጠናቸው፡፡ ከእርሷም ዘንጊዎች ነበሩ፡፡

(81) We gave them Our signs, but they kept turning away from them.

وَكَانُوا يَنْحِتُونَ مِنَ الْجِبَالِ بُيُوتًا آمِنِينَ  [82]

(82) ከኮረብታዎችም ቤቶችን ጸጥተኞች ኾነው ይጠርቡ ነበር፡፡

(82) They carved houses in the mountains, feeling secure.

فَأَخَذَتْهُمُ الصَّيْحَةُ مُصْبِحِينَ  [83]

(83) ያነጉም ሲኾኑ ጩኸት ያዘቻቸው፤ (ወደሙ)፡፡

(83) So they were seized by the blast early in the morning.

فَمَا أَغْنَىٰ عَنْهُم مَّا كَانُوا يَكْسِبُونَ  [84]

(84) ይሠሩትም የነበሩት ሕንጻ ምንም አልጠቀማቸውም፡፡

(84) Nothing of what they earned was of any avail to them.

وَمَا خَلَقْنَا السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ وَمَا بَيْنَهُمَا إِلَّا بِالْحَقِّ ۗ وَإِنَّ السَّاعَةَ لَآتِيَةٌ ۖ فَاصْفَحِ الصَّفْحَ الْجَمِيلَ  [85]

(85) ሰማያትንና ምድርንም በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በእውነት እንጂ (በላግጣ) አልፈጠርንም፡፡ ሰዓቲቱም በእርግጥ መጪ ናት፡፡ መልካምንም ይቅርታ አድርግላቸው፡፡

(85) We have not created the heavens and earth and all that is between them except for a true purpose. The Hour is certainly coming, so bear with them graciously.

إِنَّ رَبَّكَ هُوَ الْخَلَّاقُ الْعَلِيمُ  [86]

(86) ጌታህ እርሱ (ያልነበረን) ፈጣሪው ዐዋቂው ነው፡፡

(86) Indeed, your Lord is the Absolute Creator, the All-Knowing.

وَلَقَدْ آتَيْنَاكَ سَبْعًا مِّنَ الْمَثَانِي وَالْقُرْآنَ الْعَظِيمَ  [87]

(87) ከሚደጋገሙ የኾኑን ሰባትንና ታላቁንም ቁርኣን (በሙሉ) በእርግጥ ሰጠንህ፡፡

(87) We have surely given you the seven oft-repeated verses and the great Qur’an.

لَا تَمُدَّنَّ عَيْنَيْكَ إِلَىٰ مَا مَتَّعْنَا بِهِ أَزْوَاجًا مِّنْهُمْ وَلَا تَحْزَنْ عَلَيْهِمْ وَاخْفِضْ جَنَاحَكَ لِلْمُؤْمِنِينَ  [88]

(88) ከእነርሱ (ከከሓዲዎች) ብዙዎችን ወገኖች በእርሱ ወደ አጣቀምንበት ጸጋ ዓይኖችህን አትዘርጋ፡፡ በእነሱም ላይ (ባያምኑ) አትዘን፡፡ ክንፍህንም ለምእምናን አለዝብ፡፡

(88) Do not look longingly at the pleasures We have given certain classes of them, nor grieve over them, but lower your wing [in humility] to the believers.

وَقُلْ إِنِّي أَنَا النَّذِيرُ الْمُبِينُ  [89]

(89) በልም «እኔ ግልጽ አስፈራሪው እኔ ነኝ፡፡»

(89) And say, “I am indeed a clear warner.” –

كَمَا أَنزَلْنَا عَلَى الْمُقْتَسِمِينَ  [90]

(90) (ሰዎችን ለማገድ የመካን በሮች) በተከፋፈሉት ላይ እንደ አወረድነው (በኾነ ቅጣት አሰፈራሪያችሁ ነኝ በል)፡፡

(90) just as We sent down [punishment] upon those who divided [their religion],

الَّذِينَ جَعَلُوا الْقُرْآنَ عِضِينَ  [91]

(91) (እነርሱም) እነዚያ ቁርኣንንን ክፍልፍሎች ያደረጉ ናቸው፡፡

(91) those who split the Qur’an into different portions.

فَوَرَبِّكَ لَنَسْأَلَنَّهُمْ أَجْمَعِينَ  [92]

(92) በጌታህም እንምላለን፡፡ ሁላቸውንም እንጠይቃቸዋለን፤

(92) By your Lord, We will surely question them all

عَمَّا كَانُوا يَعْمَلُونَ  [93]

(93) ይሠሩት ከነበሩት ነገር ሁሉ፡፡

(93) concerning what they used to do.

فَاصْدَعْ بِمَا تُؤْمَرُ وَأَعْرِضْ عَنِ الْمُشْرِكِينَ  [94]

(94) የታዘዝክበትንም ነገር በይፋ ግለጽ፡፡ አጋሪዎችንም ተዋቸው፡፡

(94) Then proclaim what you are commanded, and turn away from those who associate partners with Allah.

إِنَّا كَفَيْنَاكَ الْمُسْتَهْزِئِينَ  [95]

(95) ተሳላቂዎችን ሁሉ እኛ በቅተንሃል፡፡

(95) We will surely suffice you against the mockers,

الَّذِينَ يَجْعَلُونَ مَعَ اللَّهِ إِلَٰهًا آخَرَ ۚ فَسَوْفَ يَعْلَمُونَ  [96]

(96) (እነሱም) እነዚያ ከአላህ ጋር ሌላ አምላክን ያደረጉ ናቸው፡፡ በእርግጥም (ፍጻሜያቸውን) ወደፊት ያውቃሉ፡፡

(96) those who set up besides Allah another god; they will come to know.

وَلَقَدْ نَعْلَمُ أَنَّكَ يَضِيقُ صَدْرُكَ بِمَا يَقُولُونَ  [97]

(97) አንተም በሚሉት ነገር ልብህ የሚጠብ መኾኑን በእርግጥ እናውቃለን፡፡

(97) We know that you are distressed by what they say.

فَسَبِّحْ بِحَمْدِ رَبِّكَ وَكُن مِّنَ السَّاجِدِينَ  [98]

(98) ጌታህንም ከማመስገን ጋር አጥራው ከሰጋጆቹም ኹን፡፡

(98) Glorify your Lord with praise and be among those who prostrate [to Him],

وَاعْبُدْ رَبَّكَ حَتَّىٰ يَأْتِيَكَ الْيَقِينُ  [99]

(99) እውነቱም (ሞት) እስኪመጣህ ድረስ ጌታህን ተገዛ፡፡

(99) and worship your Lord until the certainty [of death] comes to you.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Sorry, no related posts found.